Thursday, March 19, 2015

Meet Chef Chane, Ethiopia's Version Of The Infamous 'Soup Nazi'





 Gregory Warner/NPR
Customers line up, waiting to order from Chef Chane in Addis Ababa, Ethiopia. He runs his restaurant like a fiefdom, dispensing food and insults majestically from the kitchen, which doubles as a serving station.
I didn't travel all the way to Ethiopia just to meet a character out of the sitcomSeinfeldBut when I heard Ethiopians describe a particular popular restaurant called Chane's, I couldn't help recognize a resemblance, in its owner and lead chef, to the famously brusque soup man.
Just like his New York doppelganger, the 71-year-old Chef Chane runs a restaurant with its own unwritten rules. Rule No. 1: Come on time. Lunch is served only from 12 to 1 and he always runs out of food. Rule No. 2: Don't ask for a menu. You'll eat whatever dish the chef decided to cook that day. Rule No. 3: When you step up to the counter and face the imperious chef in his tall white hat, don't, whatever you do, hold up the line.

Tuesday, March 3, 2015

ታላቁ የአድዋ ድል

( ከበደ ደበሌ ሮቢ)

“የዓለም ታሪክ ተገለበጠ”

ከፈረሠኞች አሉ በልዩ 
መሀል አገዳ የሚለያዩ፤ 
*   *   *
አየሁት አድዋን እንደ ኮከብ ደምቆ 
የበቀለበትን ሠው መሬት ላይ ወድቆ፤ 
*   *   *
የአድዋ ሥላሤን ጠላት አረከሠው 
ገበየሁ በሞቴ ግባና ቀድሠው፤ 
*   *   *
ምኒሊክ ተወልዶ ባያነሣ ጋሻ 
ግብሩ እንቁላል ነበር ይሄን ጊዜ አበሻ፤ 
*   *   *
ገበየሁ ቢሞት ተተካ ባልቻ 
መድፍ አገላባጭ ብቻ ለብቻ፤ 
*   *   *
ታላቁ የአድዋ ጦርነት የአፍሪቃውያን ትውልዶች ታላቅ የነፃነት ተጋድሎ ነው፡፡ ሞትና ባርነት የተቀበሩበት፤ እውነትና ፍትህ አሸንፈው ህይወት የዘሩበት፡፡ 
ልክ የዛሬ አንድ መቶ አሥራ ዘጠኝ ዓመት፤ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም “ጥቁር ህዝብ ትልቅ ትል ነው ቅንቡርሥ ነው እንጂ ነፍሥ ያለው ሠው አይደለም” ብለው አፍሪቃን በሽሚያ የተቀራመቱ የአውሮጳ ቅኝ ገዢዎች ከመላው ኢትዮጵያ ዳር እስከዳር ተወጣጥቶ አድዋ በዘለቀ አንድ መቶ ሺህ የገበሬ ሠራዊት የተቆጣ ክንድ አድዋ ላይ ድባቅ ተመቱ፡፡ 
እንግሊዞች ፡- የዓለም ታሪክ ተገለበጠ፤ ታላቅ የትውልድ ኃይል አፍሪቃ ውስጥ ተቀሠቀሠ…አሉ፡፡ የታሪክ ተመራማሪው ጆርጅ በርክሌይ፤ “ኢትዮጵያውያን ባበደ መንፈሥ ተዋግተው የአውሮጳን ቅኝ ገዢዎች አሸነፉ”…በማለት ፅፈዋል፡፡ 
በመቶ ሺህ ከሚሠላው የገበሬ ሠራዊት ሃያ ዘጠኝ ሺህ የሚሆነው ፈረሠኛ ነው፡፡ በአድዋ ገመገሞች ፡- በረቢ አርእየኒ በሸልዶ ተራራ በማርያም ሸዊቶ…የሚያብረቀርቅ ጐራዴያቸውን አየር ውስጥ እየቀዘፉ፣ የጋሻቸውን እምብርት ምድር ላይ እያጠቀሡ ሠማይ ደርሠው ምድር እየተመለሡ ከሚያሽካኩ ሠንጋ ፈረሶቻቸው ጋር እየፎከሩ እየሸለሉ….ያበጠውን የአውሮጳ ኃይል የዶጋ አመድ አደረጉ፡፡ ከሌሊቱ በዘጠኝ ሠዓት ግድም የመጀመሪያዋ ጥይት ፈነዳች፡፡ የመጀመሪያዋ ጥይት የፈነዳችው ከሌሊቱ አሥራ አንድ ሠዓት ግድም ነው የሚሉ የታሪክ ሊቃውንትም አሉ፡፡ 
በቅዱሥ ጊዮርጊስ በዕለቱ ቀኑ ማልዶ የተጀመረው ከባድ ጦርነት ከቀኑ አምሥት ሠዓት አካባቢ አሸናፊውን ወይንም ድል አድራጊውን ኃይል ለየ፡፡ በወታደራዊ አካዳሚ የሠለጠነው የኢጣሊያ ቅኝ ገዢ ሠራዊት ከኢትዮጵያ የተቆጣ ጀግና የገበሬ ሠራዊት ጋር ግማሽ ቀን እንኳን በመተጋተግ ለመዋጋት አልቻለም፡፡ ከቀትር በፊት በጄኔራል ባራቴሪ የሚመራው አውሮጳዊ ሠራዊት ተፍረከረከ። 

































ከዚህ በኋላ ባለው ጊዜ ያለቀው አልቆ፣ የቆሰለው ቆሥሎ የተረፈው መሸሽ ሲጀምር ኢትዮጵያውያን ጀግኖች እያሣደዱ ፈጁት፡፡ ከሚሸሹት መሃከል አንዱ ጄኔራል ባራቴሪ ነው፡፡ ጄኔራል አልቤርቶኒ ተማርኳል፡፡ ሃምሣ ስድሥቱም የኢጣሊያ መድፎች በኢትዮጵያ የገበሬ ሠራዊት ተማርከዋል፡፡ አብዛኞቹ የኢጣሊያ ቅኝ ገዢ ወታደሮች ተገድለዋል፡፡ ጥቂቶቹ ከጄኔራል ባራቴሪ ጋር ሸሽተው ከማምለጣቸው በቀር ከሞት የተረፉት ቆሥለዋል፤ ተማርከዋል፡፡ 

Friday, February 27, 2015

ምንሊክ ……ጥቁር ሰው! The Battle of Adwa













The Battle of Adwa (also known as Adowa, or sometimes by the Italian name Adua) was fought on 1 March 1896 between the Ethiopian Empire and the Kingdom of Italy near the town of Adwa, Ethiopia, in Tigray. It was the climactic battle of the First Italo-Ethiopian War, securing Ethiopian sovereignty.
As the 20th century approached, most of Africa had been carved up among the European powers. The two independent exceptions were the young Republic of Liberia on the west coast of the continent and the Ethiopian Empire in the strategicHorn of Africa. The newly unified Kingdom of Italy was a relative newcomer to the colonial scramble for Africa. Italy had two recently obtained African territories: Eritrea and Somaliland. Both were near Ethiopia on the Horn of Africa and both were impoverished. Italy sought to improve its position in Africa by conquering Ethiopia and joining it with its two territories.

Wednesday, February 25, 2015

ከአባት አርበኛ ጋር አዝናኝ ቃለምልልስ ናፍቆት ዮሴፍ

የ95 ዓመት አባት አርበኛ ናቸው፡፡ ያልዘመቱበት የጦር አውድማ የለም። በዚህ ዕድሜያቸው ከ70 ዓመት በፊት የተደረጉ ጦርነቶችን ከእነ ዓመተምህረታቸው ያስታውሳሉ፡፡ 
ባለፈው ሳምንት በኢኮኖሚና ንግድ አምድ ላይ ቃለምልልስ የተደረገላቸው “የባላገሩ አስጐብኚ ድርጅት” ባለቤት፣ አባት አርበኞችን ወደ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ወስዶ የማስጐብኘት ሃሳብ የመጣላቸው በእኚህ አዛውንት ጥያቄ መሆኑን ገልፀውልናል፡፡ 
የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛዋ ናፍቆት ዮሴፍ ከእኚህ የዕድሜ ባለፀጋ አባት ጋር ማራኪና አዝናኝ ቃለምልልስ አድርጋለች። እነሆ:-



ስምዎትን ያስተዋውቁኝ አባት…
ሃምሳ አለቃ ደምሴ ፀጋዬ እባላለሁ፡፡ ትውልድና እድገቴ ወሎና ጎንደር ነው፡፡ በአንድ ጎን ደባት ገብርኤል ነኝ፡፡ በሌላ ጎኔ ደግሞ ወሎ ውስጥ የጁ እና ላስታ ነው እድገቴ፡፡ ጠቅለል ስታደርጊው ዘር ሃረጌ ከወሎ እና ከጎንደር ይመዘዛል ማለት ነው፡፡ 
እስቲ ስለልጅነት ያጫውቱኝ?
እንዴ! የአስተዳደጌ ሁኔታማ ምን ይወራል። የተወለድኩት በ1911 ዓ.ም ታህሳስ 3 ቀን ነው፡፡ ከዚያ ጊዜ ጀምረሽ እድሜዬን ማስላት ትችያለሽ፡፡ ጠላታችን ጣሊያን መጥቶ አባቶቻችን ሲዘምቱ የ18 ዓመት አፍላ ጎረምሳ ነበርኩኝ፤ በ1928 ዓ.ም ማለት ነው፡፡ አባቴ በውጊያው ቆስሎ ነበር ከዘመቻው የተመለሰው፡፡ 
የት ቦታ አባትዎ እንደቆሰሉ አልነገሩዎትም?
ነግሮኛል! ማይጨው ላይ ነው የተመታው፡፡ የዘመተው ከደጃዝማች አድማሱ ብሩ ጋር መሆኑንም አጫውቶኛል፡፡ ደጃዝማቹ እዚያው በውጊያው ሲሞቱ፣ አባቴ ግን ቆስሎ መጣ፡፡ የማስታውሰው እኔ የ19 ዓመት ወጣት ስለነበርኩ፣ አባቴ ውጊያ ሲሄድ የእርሻውን ስራ እኔ እሸፍን ነበር፡፡ አባቴ ከውጊያ የመጣ ቀንም ሞፈርና ቀንበሬን አነባብሬ እርሻ ወርጄ ማሽላ ስዘራ ነበር የዋልኩት፡፡ እነሱ ሲመጡ ጥይቱ እንደ ማሽላ ቆሎ… ጣ  ጣ   ጣ  ጣ ይላል፡፡ ምንድን ነው ነገሩ ብዬ ስጠይቅ፤ “አባትሽ መጣ” አሉኝ፤ አንቺ ነበር የሚሉኝ፡፡ 
ለምንድነው አንቺ የሚልዎት?
ምክንያቱ በግልፅ አይገባኝም፡፡ ስገምት ግን ስራመድ ከእግሬ እንደ ሴት ፈጠን እላለሁ፡፡ ለዚያ ይመስለኛል፡፡ 
ከዚያስ?

Monday, February 2, 2015

‹‹ልጅነቴ በሙዚቃ ተጣጥሞ አልፏል›› ፀሐይ ዮሐንስ

 ተጻፈ በ  
የፀሐይ ዮሐንስ
 ‹‹ማንበብና መጻፍ ዋናው ቁም ነገር፤ ከሕይወቴ ጐሎ እሸበር ጀመር›› የሚለው ስንኝ የብዙዎች ትዝታ ነው፡፡
በጊዜው በመሠረተ ትምህርት ዘመቻ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደነበረውም ይታመናል፡፡ ‹‹ሳብ ሳም››፣ ‹‹ተባለ እንዴ›› እና ‹‹ያላንቺማ›› የፀሐዬ (ብዙዎች እንደሚጠሩት) ስም ከሚነሳባቸው ዘፈኖች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ በተመሳሳይ ስለ ሀገር ያዜማቸውም የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ ፀሐዬ ‹‹የኔታ›› የተሰኘ አልበም በቅርቡ ለቋል፡፡ አልበሙንና አጠቃላይ የሙዚቃ ሕይወቱን በሚመለከትምሕረተሥላሴ መኰንን ከፀሐዬ ዮሐንስ ጋር ቆይታ አድርጋለች፡፡  
ሪፖርተር፡- ከመታወቅህ አስቀድሞ የሙዚቃ ሕይወትህ ምን ይመስል ነበር?
ፀሐይ፡- ጃንሜዳ አካባቢ መኖሬ ወደ ሙዚቃ ለመግባቴ ትልቁ ምክንያት ይመስለኛል፡፡ የልጅነቴን ተሰጥኦ እዛ ነው ያዳበርኩት፡፡ በምንነጋገርበት በዚህ የጥምቀት ሰሞን ብዙ ትዝታ አለኝ፡፡ ጥምቀት ለሙዚቃ ፍቅሬ መንገድ የከፈተ ነው፡፡ ያደግኩበትም ግቢ ጃንሜዳ አጠገብ ባለው ሙዚቀኛ ግቢ ነው፡፡ ጥላሁን፣ መሐሙድና ብዙነሽ የነበሩበት ክብር ዘበኛ ኦርኬስትራ ትልቁን ሚና ተጫውቷል፡፡ ጠዋት ደብተር ይዤ ሄጄ እዛ እውላለሁ፡፡ ክብር ዘበኛ ባልሠራም የክብር ዘበኛ ልጅ ስለሆንኩኝ ልጅነቴ በሙዚቃ ተጣጥሞ አልፏል፡፡ 
ሪፖርተር፡- ድምፃዊነትን ሙያዬ ብለህ ‹‹በርታ ዘመዴ››ን ከተጫወትክ በኋላስ? 
ፀሐይ፡- ያኔ ዜማ ማውጣት ጀመርኩ፡፡ ‹‹ማንበብና መጻፍ›› የኔ ዜማ ነው፡፡ አቶ ተስፋዬ ለማ አምባሳደር ቴአትርን ባቋቋሙበት ጊዜ በ1970 ዓ.ም. ከጓደኞቼ ጋር የመጀመሪያ ቅጥሬን አምባሳደር አደረግኩ፡፡ ከዛ በፊት ከክብር ዘበኛ ጋር ለዕድገት በኅብረት ዘመቻ ‹‹በርታ ዘመዴ ዘማቹ ጓዴ››ን ከሒሩት በቀለ ልጅ ጋር ሆነን ሠርተናል፡፡ ከዛ በኋላ አሻራዬ ያረፈባቸው 14 አልበሞች አሉኝ፡፡ 
ሪፖርተር፡- የመጀመሪያ አልበምህ እንዴት ነበር? 
ፀሐይ፡- ሙዚቃ ቤቶች ፕሮዲውስ ያደርጉ ስለነበር ልምድ ያለው ሰው ይፈልጋሉ፡፡ በዛ ወቅት ገና ልጅ ነኝ፡፡ ስሜት እንጂ ልምድ የለኝም፤ ስሜቴን ወደ ተግባር ለመቀየር ገንዘብ ስለሚያስወጣ ፕሮዲውሰሩ ይቸገራል፡፡ እንደ ምንም የመጀመሪያው ካሴት በሱፐር ሶኒክ ሙዚቃ ቤት አሳታሚነት ተሠራ፡፡ ጥሩ እየተሸጠ እያለ በአጋጣሚ እነ መሐሙድ አህመድና ውብሸት ፍስሐ ወደ ኤሜሪካ ከዋልያስ ባንድ ጋር ሄደው በኤሌክትሮኒክስ መሣሪያ ታጅበው ‹‹ማለዳ ማለዳ›› ያለበትን ካሴት አወጡ፡፡ ካሴቱ የእኔን ሸፈነውና ብዙ ሳይደመጥ አለፈ፡፡ በዓመቱ በንዴት ‹‹ፍንጭቷ››ን ሠራሁ፡፡ ‹‹ፍንጭቷ››ን ይዤ ስወጣ ፀሐዬ ዮሐንስ የሚለው ስምም ተገኘ፡፡ 
ሪፖርተር፡- ትንሹና ከፍተኛውስ ክፍያ ስንት ነው? 
ፀሐይ፡- ያልተለመደ ዘዬና ድምፅ ይዤ ስለመጣሁ በሽያጭ ‹‹ፍንጭቷ›› በጣም ኃይለኛ ነበር፡፡ ‹‹ሳብ ሳም››፣ ‹‹ተባለ እንዴ›› እና ‹‹ያላንቺማ›› በጣም ጥሩ ሥራዎች ነበሩ፡፡ የመጀመሪያ ክፍያዬ 3,000 ብር ነበር፡፡ እንደ ጀማሪና በወቅቱ ገንዘቡ ከነበረው ዋጋ አንፃር ትልቅ ነበር፡፡ የ300,000 ሺሕ ብር ያህል አቅም ነበረው፡፡ የመጀመሪያ ካሴት ስም ማግኛ ስለሆነ ከክፍያ ይልቅ ስም ማግኘቱ ላይ አተኩሬ ነበር፡፡ 
ጥበብን በገንዘብ መለካት አስቸጋሪ ነው፡፡ በተለይ በእኛ ሀገር በሥራውና በተሸጠው መጠን አይከፈልም፡፡ መልካም ሥራ በመሥራት መልካም ስም ነው የሚተርፈው፡፡ በ‹‹ተባለ እንዴ›› ጊዜ ክፍያው 100,000 ሺሕ ብርም ደርሶ ነበር፡፡ ከ‹‹ተባለ እንዴ›› በኋላ የካሴት ሥራ የተበላሸበት ዘመን ነው፡፡ ሰው ሸጦ የሚያተርፍበት ጊዜ አልነበረም፡፡ ኮምፒዩተር መጣና በደቂቃ ሁሉም ሰው የሚቀዳበት ደረጃ ደረሰ፡፡ ሲዲ ከመምጣቱ በፊት ሽያጭ ጥሩ ነበር፤ ከፍተኛ የገቢ ምንጭም ነበር፡፡ ኦሪጅናል ካሴት 13 ብር ይሸጥ ነበር፡፡ ለማባዛት ባዶ ካሴት አምስት ብር ማስቀጃ ሦስት ብር ነበር፡፡ አምስት ብር ጨምሮ ኦሪጅናል መግዛት ስለሚመረጥ ገበያ ነበር፡፡ ዛሬ በአንድ ፍላሽ እስከ 500 ዘፈን ስለሚያዝ ኦሪጅናል የሚገዛ የለም፡፡ አቁሞ የሚያስኬደን ከኮንሰርት የሚገኝ ገንዘብ ነው እንጂ ዛሬ የሚሠራው ለነገ አያበረታታም፡፡ ጥበቡ እየሞተ ይመስለኛል፡፡ ባወጣሁት ልክ ካላገኘሁ የመሥራት አቅሜ ይዳከማል፡፡ ዛሬ እኔ ነገ ደግሞ ሌላው ከዘርፉ ይወጣል፡፡ በ‹‹የኔታ›› አልበም ብዙ ነው ያወጣሁት፡፡ የሚመጣውና የሚገኘው ተመጣጣኝ ካልሆነ ነገ ለጥበብ ብዬ ለፍቼ ልሠራ አልችልም፡፡ አልበሙ በሙሉ ባንድ ነው የተሠራው

Friday, January 30, 2015

The State of Art in Ethiopia



የታላቁ ሜትር አርቲስት የአለም ሎርየት አፈወርቅ ተክሌ መሳጭ ንግግር በኮንግርስ  አፍ ላይብረሪ


Renowned artist Afewerk Tekle presented a lecture on the state of art in his native Ethiopia.Speaker Biography: Afewerk Tekle was one of Ethiopia's most celebrated artists, particularly known for his paintings on African and Christian.

Atse Tewodros from Atse Tewodros Project


Gabriella Ghermandi

"I will risk having my bones be shattered
I will risk having my blood flow from my body like a sea
I am willing to lose my life rather than yield an inch of my
country’s independence …
… I will fight those who have come cloaking their intentions in the
Gospel, to subjugate our land"

"Atse Tewodros", is the third track of the "Atse Tewodros Project" CD,
dedicated by Gabriella Ghermandi to Emperor Tewodros II "who
modernized Ethiopia while respecting traditions"; one of the most
beloved emperors in Ethiopian history, He was the first emperor who was not of Ethiopian royal descent. He rose to power because of his perseverance and charisma, qualities that charmed the Ethiopian people to the point that they broke with centuries-old tradition and supported his accession to the throne. He was also the emperor who fought against Queen Victoria’s army and defended Ethiopian independence in the century of African colonization.
A mix of tradition and modernity, dressed with Ethiopian pride, the CD
includes also some Shellela (war songs) as a tribute to the Arbegnoch,
the Ethiopian patriots that fought the Italian invasion between 1935
and 1941.

The project, fully independent and self financed, started in 2010 in
Addis Ababa, as a result of a collaboration among Gabriella Ghermandi,
the Ethiopian composer Aklilu Zewdy and Professor Berhanu Gezaw. It
immediately caught the interest of Michele Giuliani, an Italian
pianist and composer who is the leader of the Reunion Platz Jazz Trio.

After a successful foundraising that collected over hundreds of
donations from individuals and associations, Gabriella Ghermandi and
the Reunion Platz Trio flown to Addis and met traditional Ethiopian
musicians of the Ethiocolor Band (official group of 2014 WomaX
edition) and to complete the musical arrangements and record the CD
(in live sessions at Langano Studio, engineered by Abegasu Shiota).

Though not distributed yet, the CD already got positive reviews from
Italian and international press. This is and excerpt from fRoots: "The
music is clear, thoughtful and unforced. The contrast between
Gabriella’s warm, accurate voice and washint (flute) and dry, aching
krar (lyre) and calm, jazzy rhythm section is powerfully evocative.
Worth seek- ing out – and you will have to seek it out, being a
self-published album at present, though a label to take it up must be
likely".
http://www.worldmusic.net