Monday, November 4, 2013

“ባህላዊውን ሙዚቃ ወጣቱ እንዲወደው እፈልጋለሁ” አበባየሁ ገበያው


አብዛኛው ሙዚቃ አፍቃሪ የሚያውቀውና ዝነኝነት የተቀዳጀበት ዘፈኑ “ሰላ በይልኝ” የሚለው ቢሆንም በኢትዮጵያ ያልተለቀቁ በርካታ ዘፈኖች ያህል እንዳሉት ይናገራል - ወጣት ድምፃዊ ጐሳዬ ቀለሙ (ጃኪ ጎሲ)፡፡ ወደ ሙዚቃው ህይወት የገባው ገና በ13 ዓመቱ ነበር - በትያትር በኩል፡፡ በታዳጊነቱ ከታዋቂ አርቲስቶች ጋር ትያትር ለማሳየት ወደ ፈረንሳይ ሄዶ ለበርካታ ዓመታት ወደ አገሩ አልተመለሰም፡፡ በጀርመን በሬጌ ባንድ ውስጥ እንግሊዝኛ ዘፈኖችን ሲያቀነቅን የቆየው ጃኪ ጐሲ፤ የመጀመርያ የአማርኛ ነጠላ ዜማውን ኢትዮጵያ መጥቶ እንደሰራ ይናገራል፡፡ ባህላዊ ዘፈኖችን እያዘመነ በመስራት ወጣቱ ባህላዊውን ሙዚቃ እንዲወደው የማድረግ ፍላጐት አለው፡፡ 
በአሁኑ ሰዓት በአዲስ አበባ የመጀመርያ ሙሉ አልበሙን ለማውጣት ተፍ ተፍ የሚለው ጃኪ፤ ከአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አበባየሁ ገበያው ጋር በህይወቱና በሙዚቃ ሙያው ዙሪያ እንዲህ አውግተዋል፡-
ሥራ ላይ ነው እንዴ ያደርከው? የደከመህ ትመስላለህ ?
አዎ ፤አልበም እየሰራሁ ነው፡፡ ሙሉ አልበም የማወጣው ለመጀመሪያ ጊዜ ስለሆነ ጥሩ ስራ ለመስራት ቀን ከሌት እየተጋሁ ነው፡፡ 
ምን ዓይነት ዘፋኝ ነኝ ብለህ ነው የምታስበው? ባህላዊ ወይስ ዘመናዊ ?
አቅሜ ብዙ ነው ብዬ ነው የማስበው። ባህላዊውንም ዘመናዊንም እችላለሁ። ባህላዊ ሙዚቃን ሞደርን ለማድረግ ነው የምፈልገው፤የባህሉን ሙዚቃ ወጣቱ ትውልድ እንዲወደው እፈልጋለሁ፡፡ ባህሌን ስለምወድ ነው ወደ ባህላዊው የመጣሁት፡፡ ውጭ አገር ሬጌ ባንድ ውስጥ እንግሊዝኛ ሙዚቃ ነበር የምጫወተው፡፡ ያ ደግሞ እኔን አይገልፀኝም፤ እኔነቴን አይወክልም ብዬ ስለማምን ነው የተውኩት፡፡ በዘመናዊ ሙዚቃ ውስጥም አለሁኝ፡፡ ባህላዊ ዘፋኝ ብቻ አይደለሁም። በአዲሱ አልበሜ ባህላዊ ዘፈን ብቻ አይደለም ይዤ የምቀርበው፤አቅሜንም ለማሳየት ስለምፈልግ ለአድናቂዎቼ የተለያዩ ነገሮች ነው የማቀርበው፡፡ ኢትዮጵዊ ቀለም ያላቸው ዘመናዊ ዘፈኖችን ነው የሰራሁት፡፡

Sunday, November 3, 2013

ስብሐት ገ/ እግዚአብሔር ስንት አይነት ገጸ-ባህሪ ነው


ከበፍቃዱ አባይ

አመቱ ምንም እንኳን 2005 ዓ.ም ላይ ቢሆንም በቅርቡ ልንለው በምንችለው መልኩ ላንባብያን የደረሰውንና ስብሐት ገ/እግዚእብሔርን የተመለከተውን መጽሐፍ አነበብኩት፡፡ስለመጽሕፉና በውስጡ ስለተካተቱ የተለያዩ መልከ-ስብሐት ሐሳቦችን አስመልከቶም በተለያዩ የህትመት ውጤቶች ላይ የቀረቡ ክርክሮችንም ሳነብ ቆይቻለሁ፡፡ በመጽሐፉ ላይ ከተካተቱት የስብሐት መልኮች ውስጥ ግዝፍ ነስቶ የበርካታ አንባብያንን ቀልብ ለመሳብ የቻለው የአርክቴክቱ ሚካኤል ሽፍራው ስብሐትን ከሌላ ማዕዘን የተሰኘው እይታ ነው ለማለት ይቻላል፡፡ በዚህ ሐሳብ ዙሪያ ታድያ የቀረቡት በርካታ ክርክሮችም ውሐ የሚያነሱ ሆነው አግኝቻቸዋለሁ፡፡ እኔም ስለ መልክአ-ስብሐት ያለኝን አተያይ ለመከተብ ጊዜ ያላጠፋሁ ቢሆንም ለአደባባይ መብቃቱ ላይ ግን ሰንፌ ቆይቻለሁ ዛሬም ሰዓቱ ባለመርፈዱ ስለ መጽሐፉ ጥቂት ለማለት ወድጃለሁ፡፡
መልክዐ ሰብሐት የሚል ስያሜ ያለው ይህ መጽሐፍ በ30 ጸሐፍት፤ደራስያንና ሰዓሊያን እንደተጻፈ የጀርባ ሽፋኑ ላይ የተገለጠ ቢሆንም እኔ ግን በቆጠራ የደረስኩበት 27 ባለሙያዎች የተሳለፉበት መሆኑን ነው፡፡ያም ሆነ ይህ ግን ስበሐት በሐገራችን ካሉ በጣት ከሚቆጠሩ ስመ ጥር ደረስያን/ት/መሐከል እጅግ እድለኛውና በተለያዩ ጸሀፍት ሊዘክር የበቃ ደራሲና ተርጓሚ ነው ለማለት እችላለሁ፡፡በህይወት በነበረበት ወቅት በተለያዩ ወጣቶች ልደቶቹ የተከበሩለት፤በታላላቅ መደረኮች ለመታደም የቻለ፤ከህልፈቱም በኋላም ሆነ በፊት በስሙ ጥቂት የማይባሉ ስነ-ጽሑፋዊ በረከቶች የተለገሱለት ኢትዮጽያዊ ነው፡፡ሰሞነኛው መልክአ ሰብሐትም አንግዲህ የዚህ የሰውየው ስም መነሻ ለመሆን የበቃ መጽሐፍ ነው፡፡ለስብሐት ከፍ ያለ ፍቅርና አክብሮት ያላቸው ጸሐፍት፤ገጣምያንና ሰዓሊያን የታደሙበት መጽሐፍ ታድያ በአብዛኛው ወደ መወድስ ስብሐት ያደሉ ናቸው ለማለት ይቻላል፡፡ጸሐፍቱ ለስብሐት ያላቸውን ክብርና ፍቅር ለመግለጽም የክብር ዶክትሬት የሚገባው ስለመሆኑም ጭምር በስራዎቻቸው ላይ ወትውተዋል፡፡ ከዳኛቸው ወርቁ እስከ ሲግመንድ ፍሩድና ቻርልስ በግዴይር፤ከሄሚንጉዌ አስከ ሆቺሚኒ ደረስ ስማቸው በተወሳበት በዚህ መጽሐፍ ላይ የተለያዩ ሐሳቦች ሰፍረዋል፡፡ከዚህ በተለየ መልኩ የስብሐትን መልክ ፍጹም በማጠየምና በድፍረት ሌላ የተጠየቃዊ ሐሳበ ትንታኔ ይዞ ለመምጣት የደፈረው አርክቴክቱ ሚካኤል ሽፈራው ብቻ ነው፡፡ይህ የሚካኤል ስራ መኖርም ነው የመጽሐፉን ርዕስ ሙሉ ይሆን ዘንድ ያስቻለው፡፡እንደሌሎቹ የስብሐት መልክ ገለጻ ቢሆን ኖሮ የመጽሐፉ ርዕስ ከመልከአ ስብሐት ይልቅ ለመወድሰ ሰብሐት የቀረበ ይሆን ነበር፡፡ይህ መጽሐፍ ሰሞኑንም በጣይቱ ሆቴል ጃዝ አምባ ላውንጅ በርካታ የስብሐት አድናቂዎችና የአርታኢው አለማየሁ ገላጋይ ተጠረዎች በታደሙበት ተመርቋል፡፡በዕለቱም ከቱባ የስነ-ጽሁፍ ሰዎች እስከ ወጣቶቹ ጭምር በመድረኩ ላይ ስለ መልክአ ሰብሀት መጽሀፍ ምረቃ ሲሉ ስለ ስብአት ለአብ የተለያዩ ስራዎቻቸውን አቅርበዋል፡፡49 የኢትዮጽያ ብር የተተመነለትንና 277 ገጾችን በጉያው የሸከፈውን መልክአ ስብሀት ብዙዎች እንደሚያነቡት ተስፋ አድርጋለሁ፡፡
ከንባባችን በመለስም መጽሀፉን አንብበን ስናበቃ የምንነጋገርባቸው የሐሳብ ሰበዞችን ማቀበሉ እንደማይቀርም እገምታለሁ፡፡ይህንን መንደርደሪያ ምርኩዝ በማድረግም መጽሐፉ ለገበያ መቅረቡ በፊትም ሆነ ከረበ በኋላ ስብሐት ገ/እግዚአብሔርን አስምልከቶ ለራሴ ስጥይቃቸው የነበሩ ጥያቄዎቼን ይበልጥ ያቀጣጠሉ መግፍኤ ሐሳቦችን አነሳ ዘንድ አነሆ አልኩ፡፡
ግለ-ምልከታ

Friday, November 1, 2013

The greatest athletes of all time appear together in a short film about Ethiopian running.


Shot in Adis Ababa, Haile Gebrselassie, Kenenisa Bekele, Tirunesh Dibaba and Meseret Defar tell the story of distance running in Ethiopia. Talking ahead of this year's Bupa Great North Run, the athletes explain what it means to win a gold medal in Ethiopia, and what it takes to be the best in the world.

Haile Gebrselassie is a two time Olympic Gold Medallist, winning the 10,000m at the Atlanta and Sydney Olympic Games. Kenenisa Bekele won the Olympic 10,000m in Athens and Beijing, where he also won the 5,000m. Meseret Defar won the 2004 and 2012 Olympic 5000m titles, and Tirunesh Dibaba won the 5,000 and 10,000m at the Beijing Games and the 10,000 at London 2012. Between them they have broken dozens of World Records, and taken dozens of World Titles on the track and country.