Tuesday, March 31, 2015

ፋኖስና ብርጭቆ


አንድ የፋኖስ መብራት በግብሩ የኮራ፤
እንዲህ ሲል ተጣላ ከብርጭቆ ጋራ፡፡
‹‹እኔ ነኝ መብራቱ ብርሃን የምሰጥ፤
ጨለማን አጥፍቼ የምገላልጥ፡፡
አንተ ግን ከፊቴ እንዲህ ተደንቅረህ፤
ዙሪያዬን ከበኸኝ እንዲያው ተገትረህ፡፡
አልገባኝም ከቶ የምትሰራው ስራ፤
ብርሃኔ ሩቅ ደርሶ ደምቆ እንዳያበራ፤
አንተን ፈጠረብኝ መንገድ የምትዘጋ፡፡
እንቅፋት እየሆንክ ስራዬን አታጥፋ
ገለል በል ከፊቴ ብርሃኔ ይስፋፋ፡፡››
‹‹አገልግሎቴማ ከሆነብኝ ጥፋት፤
እውነት ላንተ ከሆንኩህ እንቅፋት፡፡
ልሂድልህ›› ብሎ ሲለቅለት ቦታ፤
ከጎን የነፈሰ የንፋስ ሽውታ፣
መጣና መብራቱን አጠፋው ባንዳፍታ፡፡
አጭር እየሆነ ተመልካችነቱ፣
መለየት አቅቶት ጥቅሙን ከጉዳቱ፣
እወቁኝ እወቁኝ እያለ ሲነሳ
ሰውም እንደዚሁ ያመጣል አበሳ፡፡

(/ ከበደ ሚካኤል)

Monday, March 30, 2015

"ከዝንጀሮም እንገኝ ከአዳምና ሄዋን ወንድምና እህት ነን» የክብር ዶ/ር ዙምራ ኑሩ"

በቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
አንጋፋው የአውራምባ ማህበረሰብ መስራች የክብር ዶክተር ዙምራ ኑሩ እሱ «ምንም እንዳልሰራሁ ሁኖ ይሰማኛል» ቢልም ሀሳቡ መሬት ወርዶ ፣ ዘር አፍርቶ ከዜሮ ቀና ወደ ማለት ሲጓዝ አይቷል ። እርሱ በቁሙ እያለ ማህበረሰቡ በንቀትና በጥላቻ ከመታየት ወጥቶ እንደ አንድ የባህል ቅርስ ሊጎበኝ በቅቷል ። በራሱ የህይወት ፍልስፍና ማህበረሰቡን ያነፀው ይህ ሰው ለእኛ ባይደንቀንም ነጮቹ ግን ህይወትና ፍልስፍናው አስደምሟቸው የክብር ጥሪ ያደርጉለታል ። ከወራት በፊት ከጥሪዎቹ አንዱን ተቀብሎ ፈረንሳይ ውስጥ የክብር ጉብኝት አድርጎ በ10 ቀናት ቆይታው በሔደበት የተናገረው ከቁም ነገር ተቆጥሮለት በፈረንሳይኛና በእንግሊዘኛ ቋንቋዎች ዶክመንታሪ ተሰርቶለት ተመልሷል ። በተመሳሳይም ከተለያዩ ሀገራት የጉብኝት ጥያቄ ይቀርብላታል ።
ዙምራ ሰሞኑን አዲስ አበባ በመጣ ጊዜ አግኝቶኝ የመጣበትን ጉዳይ ከተወያየን በኋላ ለኢትዮ ዴይሊ ፖስት ዌብ ሳይት አንባብያን የሚከተለውን አውግተናል ፡፡
zumera






















 ኢትዮ ዴይሊ ፖስት ፡- ዙምራ አዲስ አበባ እንዴት መጣህ ?
 ዙምራ፡- በመኪና ተሳፍሬ ነዋ ።
 ኢትዮ ዴይሊ ፖስት፡ በመኪናማ ነው ። ለምን አላማ መጣህ ማለቴ ነው እንጂ ።
 ዙምራ፡- አላማዬ ብዙ ነው ። እናንተ ጋዜጠኞችንም ልወቅሳችሁ ነው የመጣሁ ።
 ኢትዮ ዴይሊ ፖስት፦ ምን አደረግን ?
  ዙምራ፡- ጥሩነትና መጥፎነትን አበጥራችሁ ሕዝቡ ልብ ውስጥ አላደረሳችሁም ። ሰው በጥሩው ብቻ አይማርም ።    ከክፋትም ይማራል ። የእናንተ ድርሻ ፣ የምሁራኑም ድርሻ ክፉ ከደግ እንዲለይና እንዲታይ ማድረግ ነው ፡፡     እናንተ ናችሁ ሀገርን የምትለውጡት ። እናንተ ናችሁ ሀሳብን በጥሩ መሬት ላይ እንዲዘራ የምታደርጉ ። ይህን ነው የምጠይቃችሁ ። እናንተ መልካም ዘር ናችሁ ብላችሁ አምናችሁ መች ወደሰው አደረሳችሁን መች ሀሳባችን ሰውጋ ደረሰ 

Tuesday, March 24, 2015

የህፃናት አምባ ልጆች ትዝታና ቁጭት

Written by  መታሰቢያ ካሳዬ
  ወቅቱ 1973 ዓ.ም ነበር፡፡ አገሪቱ ከተለያዩ የውስጥና የውጪ ኃይሎች ጋር ጦርነት ውስጥ የገባችበት ጊዜ ነው፡፡ በርካታ ኢትዮጵያውያን ወታደሮች ልጆቻቸውን ያለ አሳዳጊ ጥለው በየጦር ሜዳው ወድቀዋል፡፡ አሳዳጊና ተንከባካቢ ያጡት ህፃናት በየጎዳናው መውደቃቸው ያሳሰበው የደርግ መንግስት፤ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት በነበሩት መንግስቱ ኃይለማርያም ልዩ ትዕዛዝ የአብዮታዊት ኢትዮጵያ ህፃናት አምባ ተቋቁሞ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ 
በቀድሞ አጠራር በሸዋ ክፍለ ሃገር ሀይቆችና ቡታጅራ አውራጃ፣ በአላባ ቁሊቶ ወረዳ፣ አላጌ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ወላጆቻቸውን በጦርነትና በሌሎችም ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ አደጋዎች ያጡ ህፃናትን ተቀብሎ መሰረታዊ ፍላጎቶቻቸውን በማሟላት፣ በትምህርትና በሥነ ምግባር ኮትኩቶ የማሳደግን ዓላማ አንግቦ የተቋቋመው አምባው፤ “ሰብለ አብዮት”፣ “መስከረም ሁለት ኦጋዴን”፣ “ዘርዓይ ደረስ” እና “መንግስቱ ኃ/ማርያም” በተባሉ 5 መንደሮች የተከፋፈለ ነበር፡፡ 
አምባው ገና ከተወለዱ ህፃናት ጀምሮ በተለያዩ የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ህፃናትን ተቀብሎ እያሳደገ ያስተምርና ዕድሜያቸው 18 ዓመት ሲሞላ (የ12ኛ ክፍል ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁ) ከማሳደጊያው ይሰናበታሉ፡፡ ህፃናቱ አምባውን ለቀው በሚወጡ ጊዜ በስነ ምግባር የታነፁ እንዲሆኑና በማህበራዊ ህይወታቸውም የመገለል ስሜት እንዳያድርባቸው ልዩ የምክር አገልግሎት ይሰጣቸው እንደነበር የቀድሞው የአምባው ልጆች ያስታውሳሉ፡፡ በትምህርታቸው ጥሩ ውጤት ያገኙ ተማሪዎች አንድም ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ይገባሉ አሊያም ወደ ውጪ አገር (በአብዛኛው ኩባና ራሺያ) እየሄዱ ይማሩ ነበር፡፡ በ1983 ዓ.ም የአምባው መስራችና ህፃናቱ ሁሉ ”አባታችን“ እያሉ የሚጠሯቸው የአገሪቱ መሪ ፕሬዚዳንት መንግስቱ ኃ/ማርያም አገር ጥለው መውጣት ለአምባው ህፃናትና ሰራተኞች ትልቅ ዱብ እዳ ነበር፡፡ 
የአምባው ህፃናት መሳጭና መልእክት አዘል በሆኑት ህብረ ዝማሬዎቻቸው በእጅጉ ይታወቁ ነበር፡፡ በታዋቂዋ ገጣሚ አለምፀሐይ ወዳጆ ክትትልና የጥበብ ስልጠና ይደረግላቸው የነበሩት የአምባው ልጆች፤ “የጀግና ፍሬ” በተሰኘ የኪነት ቡድን ታቅፈው በየጊዜው ለታዳሚዎች የተለያዩ ኪነ ጥበባዊ ዝግጅቶችን ያቀርቡ ነበር፡፡ በዚህ ቡድን ተዘጋጅተው ለአድማጭ ጆሮ ከበቁትና ተወዳጅነትን ካገኙት ስራዎቻቸው መካከል “ፀሐዬ”፣ “የጀግና ልጅ ጀግና” እና “እርግቢቱ ሂጂ” የሚሉት ይጠቀሳሉ፡፡ 
በ1970ዎቹ መገባደጂያና በሰማንያዎቹ መጀመሪያ ላይ አብዛኛው ታዳጊ እኒህን መዝሙሮች ከህዝብ መዝሙር ባልተናነሰ ያውቃቸው ነበር፡፡ በቀድሞዎቹ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ጣቢያዎችም መዝሙሮቹን በተደጋጋሚ መስማት አዲስ ነገር አልነበረም፡፡ የደርግን ውድቀት ተከትሎ ግን መዝሙሮቹ ታሪክ ሆነው ተረሱ፡፡ ከብዙ ዓመታት በኋላም በቅርቡ እኒህ ሥራዎች በከፊል የተካተቱበት ሲዲ ታትሞ መውጣቱ ተሰምቷል፡፡ 
እኔም አጋጣሚውን በመጠቀም የሙዚቃ ሥራው አስተባባሪ የሆኑትንና የአምባው ልጆች የነበሩትን መቅደስ ተመስገን እና ጆኒ መርጊያ ስለ ህፃናት አምባው፣ ስለ አስተዳደጋቸው፣ በተለይ ከፕሬዚዳንት መንግስቱ ጋር ስለነበራቸው ቁርኝትና ከአገር መውጣታቸውን ሲሰሙ ስለተፈጠረባቸው ስሜት እንዲሁም ስለ መዝሙሮቻቸው እንዲያወጉኝ ጠየቅኋቸው፡፡ በደስታ ፈቃደኝነታቸውን ገለፁልኝ። 

Friday, March 20, 2015

የሻምበል አበበ ቢቂላ ድምጽ














ሻምበል አበበ ቢቂላ  ለኢትዮጵያና ጥቁር አፍሪቃ የመጀመሪያውን የኦሊምፒክ ማራቶን ወርቅን ከዓለም ክብረ ወሰን ጋር ያስገኘ ኢትዮጵያዊ ከመሆኑም ሌላ በሮማ የኦሊምፒክ ውድድር በባዶ እግሩ ሮጦ በማሸነፉ፤ በተከታዩ የቶክዮ ኦሊምፒክ የራሱን የዓለም ክብረ ወሰን በማሻሻል ለሁለተኛ ጊዜ የወርቅ ሜዳይ በመሸለሙ ታሪካዊና ዝነኛ ለመሆን አብቅቶታል። 
http://am.wikipedia.org/ 

Thursday, March 19, 2015

Meet Chef Chane, Ethiopia's Version Of The Infamous 'Soup Nazi'





 Gregory Warner/NPR
Customers line up, waiting to order from Chef Chane in Addis Ababa, Ethiopia. He runs his restaurant like a fiefdom, dispensing food and insults majestically from the kitchen, which doubles as a serving station.
I didn't travel all the way to Ethiopia just to meet a character out of the sitcomSeinfeldBut when I heard Ethiopians describe a particular popular restaurant called Chane's, I couldn't help recognize a resemblance, in its owner and lead chef, to the famously brusque soup man.
Just like his New York doppelganger, the 71-year-old Chef Chane runs a restaurant with its own unwritten rules. Rule No. 1: Come on time. Lunch is served only from 12 to 1 and he always runs out of food. Rule No. 2: Don't ask for a menu. You'll eat whatever dish the chef decided to cook that day. Rule No. 3: When you step up to the counter and face the imperious chef in his tall white hat, don't, whatever you do, hold up the line.

Tuesday, March 3, 2015

ታላቁ የአድዋ ድል

( ከበደ ደበሌ ሮቢ)

“የዓለም ታሪክ ተገለበጠ”

ከፈረሠኞች አሉ በልዩ 
መሀል አገዳ የሚለያዩ፤ 
*   *   *
አየሁት አድዋን እንደ ኮከብ ደምቆ 
የበቀለበትን ሠው መሬት ላይ ወድቆ፤ 
*   *   *
የአድዋ ሥላሤን ጠላት አረከሠው 
ገበየሁ በሞቴ ግባና ቀድሠው፤ 
*   *   *
ምኒሊክ ተወልዶ ባያነሣ ጋሻ 
ግብሩ እንቁላል ነበር ይሄን ጊዜ አበሻ፤ 
*   *   *
ገበየሁ ቢሞት ተተካ ባልቻ 
መድፍ አገላባጭ ብቻ ለብቻ፤ 
*   *   *
ታላቁ የአድዋ ጦርነት የአፍሪቃውያን ትውልዶች ታላቅ የነፃነት ተጋድሎ ነው፡፡ ሞትና ባርነት የተቀበሩበት፤ እውነትና ፍትህ አሸንፈው ህይወት የዘሩበት፡፡ 
ልክ የዛሬ አንድ መቶ አሥራ ዘጠኝ ዓመት፤ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም “ጥቁር ህዝብ ትልቅ ትል ነው ቅንቡርሥ ነው እንጂ ነፍሥ ያለው ሠው አይደለም” ብለው አፍሪቃን በሽሚያ የተቀራመቱ የአውሮጳ ቅኝ ገዢዎች ከመላው ኢትዮጵያ ዳር እስከዳር ተወጣጥቶ አድዋ በዘለቀ አንድ መቶ ሺህ የገበሬ ሠራዊት የተቆጣ ክንድ አድዋ ላይ ድባቅ ተመቱ፡፡ 
እንግሊዞች ፡- የዓለም ታሪክ ተገለበጠ፤ ታላቅ የትውልድ ኃይል አፍሪቃ ውስጥ ተቀሠቀሠ…አሉ፡፡ የታሪክ ተመራማሪው ጆርጅ በርክሌይ፤ “ኢትዮጵያውያን ባበደ መንፈሥ ተዋግተው የአውሮጳን ቅኝ ገዢዎች አሸነፉ”…በማለት ፅፈዋል፡፡ 
በመቶ ሺህ ከሚሠላው የገበሬ ሠራዊት ሃያ ዘጠኝ ሺህ የሚሆነው ፈረሠኛ ነው፡፡ በአድዋ ገመገሞች ፡- በረቢ አርእየኒ በሸልዶ ተራራ በማርያም ሸዊቶ…የሚያብረቀርቅ ጐራዴያቸውን አየር ውስጥ እየቀዘፉ፣ የጋሻቸውን እምብርት ምድር ላይ እያጠቀሡ ሠማይ ደርሠው ምድር እየተመለሡ ከሚያሽካኩ ሠንጋ ፈረሶቻቸው ጋር እየፎከሩ እየሸለሉ….ያበጠውን የአውሮጳ ኃይል የዶጋ አመድ አደረጉ፡፡ ከሌሊቱ በዘጠኝ ሠዓት ግድም የመጀመሪያዋ ጥይት ፈነዳች፡፡ የመጀመሪያዋ ጥይት የፈነዳችው ከሌሊቱ አሥራ አንድ ሠዓት ግድም ነው የሚሉ የታሪክ ሊቃውንትም አሉ፡፡ 
በቅዱሥ ጊዮርጊስ በዕለቱ ቀኑ ማልዶ የተጀመረው ከባድ ጦርነት ከቀኑ አምሥት ሠዓት አካባቢ አሸናፊውን ወይንም ድል አድራጊውን ኃይል ለየ፡፡ በወታደራዊ አካዳሚ የሠለጠነው የኢጣሊያ ቅኝ ገዢ ሠራዊት ከኢትዮጵያ የተቆጣ ጀግና የገበሬ ሠራዊት ጋር ግማሽ ቀን እንኳን በመተጋተግ ለመዋጋት አልቻለም፡፡ ከቀትር በፊት በጄኔራል ባራቴሪ የሚመራው አውሮጳዊ ሠራዊት ተፍረከረከ። 

































ከዚህ በኋላ ባለው ጊዜ ያለቀው አልቆ፣ የቆሰለው ቆሥሎ የተረፈው መሸሽ ሲጀምር ኢትዮጵያውያን ጀግኖች እያሣደዱ ፈጁት፡፡ ከሚሸሹት መሃከል አንዱ ጄኔራል ባራቴሪ ነው፡፡ ጄኔራል አልቤርቶኒ ተማርኳል፡፡ ሃምሣ ስድሥቱም የኢጣሊያ መድፎች በኢትዮጵያ የገበሬ ሠራዊት ተማርከዋል፡፡ አብዛኞቹ የኢጣሊያ ቅኝ ገዢ ወታደሮች ተገድለዋል፡፡ ጥቂቶቹ ከጄኔራል ባራቴሪ ጋር ሸሽተው ከማምለጣቸው በቀር ከሞት የተረፉት ቆሥለዋል፤ ተማርከዋል፡፡