Tuesday, April 14, 2015

የትንሳኤ ስጦታ! የብላቴናው አስደማሚ ሰብዓዊ ተግባር

 Written by  አለማየሁ አንበሴ



   በየሁለት ሣምንቱ እሁድ መርካቶ አንዋር መስጊድ አካባቢ 4 ሰአት ግድም የደረሰ ማንም ሰው አንድ የተለየ ክስተት መመልከቱ አይቀርም፡፡ ነገሩ አዲስ የሚሆንበት ለእንደኔ ዓይነቱ እንግዳ እንጂ የአካባቢው ነዋሪዎችማ ለምደውታል፡፡ ላለፉት ሦስት ዓመታት ሲካሄድ የቆየ አስደማሚም አስገራሚም ሰብዓዊ ተግባር ነው፡፡ ከልጅነቱ ጀምሮ በአካባቢው የሚታወቀው ብላቴናው አስመሮም ተፈራ፤ በመርካቶ ዙሪያ በየጎዳናው የወደቁ የአዕምሮ ህሙማንን እያነሳ ገላቸውን ያጥባቸዋል፡፡ ፀጉራቸውን ይላጫቸዋል፡፡ አዲስ ልብስ ያለብሳቸዋል፡፡ ምግብም ያበላቸዋል፡፡ 
የአዕምሮ ህሙማኑን የሚያጥብበት ሰወር ያለ ስፍራ ባለመኖሩ አውራጐዳና ላይ እርቃናቸውን ሲያጥባቸው ማየት የተለመደ ትዕይንት ነው፡፡
አስመሮምን ከልጅነቱ ጀምሮ እንደሚያውቁት  የሚናገሩት የ70 ዓመቱ የአካባቢው አዛውንት አቶ መሃመድ ጀማል፤ “ሰፈር ውስጥ ሲላላክልንና ሲያገለግለን ያደገ ልጅ ነው፤ አሁንም ሰዎች የሚፀየፏቸውን የአዕምሮ ህሙማን ለመንከባከብ የሚያደርገው ጥረት የታዛዥነቱና የቀናነቱ ነጸብራቅ ነው” ይላሉ፡፡ በልጅነቱ ከቤተሰቦቹ ተለይቶ በችግር ማደጉን እናውቃለን ያሉት አዛውንቱ፤ ያለፈበትን ህይወት አስታውሶ እነዚህን ምስኪኖች በሽታ አለባቸው፣ ተባያቸው ይተላለፍብኛል ሳይል ላለፉት ሦስት ዓመታት በቋሚነት ሲያጥባቸው፣ ሲያለብሳቸውና ሲመግባቸው ተመልክቻለሁ” ሲሉ እማኝነታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ብላቴናው አስመሮም (ባሪያው) የተወለደው ከረዩ ሰፈር ቢሆንም ከቤተሰቦቹ ጋር በተፈጠረው አለመግባባት ገና የ8 ዓመት ህፃን ሳለ ነበር ወደ ጎዳና የወጣው፡፡ የአሜሪካን ግቢ ነዋሪዎች ባደረጉለት ድጋፍም በልጅነቱ በተለያዩ ስራዎች ላይ ለመሰማራት እንደቻለ ይናገራል። አስመሮም በየሁለት ሳምንቱ እሁድ ገላቸውን የሚያጥባቸው፣ ፀጉራቸውን የሚላጫቸውና ልብሳቸውን የሚቀይርላቸው እንዲሁም ምግብ የሚያበላቸው የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር 25 ደርሰዋል፡፡ በዚህም የተነሳ እየተሳቀቅሁ በአደባባይ ርቃናቸውን ሳጥባቸው ተገድጄአለሁ ይላል፡፡ ይሄን ሰብዓዊ ተግባር ለመፈፀም ወጪው ከፍተኛ እንደሚሆን መገመት አያዳግትም፡፡ እሱ ደግሞ መኪና አጥቦ አዳሪ ነው፡፡
አስመሮም እንደሚለው፤ የታክሲ ሹፌሮች ባይኖሩ ኖሮ ይሄን በጐ ተግባር ለማከናወን አይችልም ነበር፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ ባለፈው እሁድ በስፍራው ተገኝቶ ለህሙማኑ የሚደረገውን እንክብካቤ ከተመለከተ በኋላ ከወጣት አስመሮም ተፈራ ጋር በሰብዓዊ ተግባሩ ዙሪያ ተከታዩን አስገራሚና አስደማሚ ቃለምልልስ አድርጓል፡፡ 

Monday, April 6, 2015

ኢትዮጵያዊው ዶ/ር ኤሌክትሮን “የዓለማችን ልዩ ስም” ውድድርን እየመሩ ነው

ከኦባማ ቀጥሎ በአሜሪካ ከፍተኛው ደመወዝ ተከፋይ ነበሩ
ከ2ሺ በላይ የተሳኩ ቀዶ ህክምናዎችን አከናውነዋል 
ወንድሞቻቸው፡- ፕሮቶን፣ ኒውትሮን፣ ዲዩትሮን፣ ኤሌክትሮን እና ፖሲትሮን ይባላሉ

















ትውልደ ኢትዮጵያዊው ዶክተር ኤሌክትሮን ክበበው፤ ለ33ኛ ጊዜ በመካሄድ ላይ በሚገኘው የ2015 “የዓመቱ የዓለማችን ልዩ ስም” ውድድር ላይ ከፍተኛ ድምጽ በማግኘት በቀዳሚነት እየመሩ እንደሆነ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል፡፡
በአለማቀፍ ደረጃ በሚካሄደው በዚህ ውድድር ላይ ዘንድሮም የተለያዩ አገራት ዜጎችና በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ላይ የተሰማሩ 64 ግለሰቦች ያልተለመዱ ስሞች ለውድድር የቀረቡ ሲሆን ኢትዮጵያዊው ዶ/ር ኤልክትሮን ክበበው፤ በ1ሺህ 132 ድምጽ፣ በ89.6 በመቶ ውጤት በቀዳሚነት በመምራት ላይ ይገኛሉ፡፡
በኢሜልና በተለያዩ መንገዶች ከቀረቡለት በርካታ ለየት ያሉ ስሞች 64 ያህሉን በመምረጥ፣ ለአንድ ሳምንት ያህል በድረ ገጽ አማካይነት ድምጽ እንዲሰጥባቸው የሚያደርገው የውድድር ኮሚቴው፤ የመጨረሻውን ውጤት ከጥቂት ቀናት በኋላ ይፋ እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡
የሰማይ እንሽላሊት፣  ጣፋጭ ቡና፣ ዳላስ፣ ቶክዮ፣ ቴኒስ እና የመሳሰሉ የአገር፣ የቦታ፣ የእቃ፣ የሰብል ወዘተ መጠሪያዎችን የያዙ የተለያዩ አገራት ዜጎች በዘንድሮው ውድድር እንደተሳተፉ አወዳዳሪዎቹ ገልጸዋል፡፡
በዘንድሮው ውድድር ከፍተኛ ድምጽ በማግኘት በመምራት ላይ ለሚገኙት የ47 አመቱ ዶ/ር ኤሌክትሮን ይህን ስም ያወጡላቸው፣ ኤሌክትሪካል ኢንጂነር የሆኑት ኢትዮጵያዊው አባታቸው አቶ ክበበው ነበሩ፡፡
ልጆቻቸው የእሳቸውን ፈለግ ተከትለው በሳይንሱ ዘርፍ ላይሰማሩ ይችላሉ የሚል ስጋት ያደረባቸው አቶ ክበበው፤ በልጆቻቸው ልቦና ውስጥ ገና በለጋ እድሜያቸው የሳይንስን ስሜት ለማስረጽ በማሰብ ነው፣ ባልተለመደ ሁኔታ ለልጆቻቸው ከኤሌክትሪሲቲ ጋር የተያያዙ ስሞችን ያወጡት፡፡
አቶ ክበበው፤ ለአምስቱ ልጆቻቸው ፕሮቶን፣ ኒውትሮን፣ ዲዩትሮን፣ ኤሌክትሮን እና ፖሲትሮን የሚሉ ስሞችን አውጥተዋል፡፡ ዶ/ር ኤሌክትሮን በስማቸው ብቻ አይደለም የሚለዩት፡፡ ከስማቸው በላይ ብዙዎችን ያስገረመው፣ በህክምና ሙያቸው የአሜሪካ መንግስት የሚከፍላቸው ዳጎስ ያለ ደመወዝ ነው ይላል ድረ-ገጹ፡፡
ከአራት አመታት በፊት “ዊኪኦርግቻርትስ” የተባለ ተቋም “የአመቱ የአሜሪካ መንግስት 1000 ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋዮች” በሚል ባወጣው ዝርዝር ውስጥ፣ ዶ/ር ኤሌክትሮንን ከአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ቀጥሎ ከፍተኛ ደመወዝ የሚያገኙ የመንግስት ሰራተኛ በማለት በሁለተኛነት አስቀምጧቸዋል፡፡
በአዲስ አበባ በሚገኘው ቅዱስ ዮሴፍ ትምህርት ቤት የተማሩት ዶ/ር ኤሌክትሮን ክበበው፤ በአሜሪካ ሳንፍራንሲስኮ ከሚገኘው ዪኒቨርሲቲ ኦፍ ካሊፎርኒያ በህክምና የተመረቁ ሲሆን የአሜሪካን ቦርድ ኦፍ ሰርጀሪን የቀዶ ህክምና ሰርተፊኬትም አግኝተዋል፡፡ 
ላለፉት 20 አመታት በሳንፍራንሲስኮ በኢንዶክሪንና ታይሮይድ ካንሰር ዘርፍ የአጠቃላይ ቀዶ ህክምና አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙት ዶክተሩ፤ በአሜሪካ ብሄራዊ የካንሰር ኢንስቲትዩት፣ የካንሰር ምርምር ማዕከል የኢንዶክራይን ኦንኮሎጂ ቅርንጫፍ ሃላፊ ሲሆኑ የካንሰር ጄኔቲክስ ክፍሉንም በበላይነት በመምራት ላይ ይገኛሉ፡፡
ዶክተሩ በእስካሁኑ የሙያ ዘመናቸው ከሁለት ሺህ በላይ የተሳኩ ቀዶ ህክምናዎችን ያከናወኑ ሲሆን ከ150 በላይ የጥናት ጽሁፎችንና መጽሃፍትን ለህትመት እንዳበቁ “ብሬኪንግጎቭ” የተሰኘ ድረገፅ አመልክቷል፡፡
http://www.addisadmassnews.com/

Thursday, April 2, 2015

Letter from Ethiopia: back and forth

Philip Rayner
Despite breakneck economic regeneration, Addis Ababa retains many of its familiar charms and frustrations






















A busy market contains all the sights, sounds and smells of Addis Ababa. Photograph: Robert Harding World Imagery/Alamy

I am not sure why I like Ethiopia so much. In part, I think it is the sights, sounds and smells that are so evocative. Watching a blood-red sun beginning to set through the haze that hovers over Addis Ababa, watching the black kites swoop between the buildings, listening to the sounds of traffic, Ethiopian pop music and the odd chicken or two, plus the smells of wood smoke, roasting coffee, cheap diesel and something else, indescribable, but essentially African, I remember why I like this country so much.

I am also attracted by the people. In most Ethiopians there is a joy and optimism. They believe that they are on the cusp of great things: becoming a middle-income country, surfing the “knowledge superhighway”. Every state company and organisation now has a vision and mission that they publicise. I noticed that at Mekelle airport their vision was to become “the best airport in Africa”; several Ethiopian universities share the vision to become “the best university in Africa”. There is no sense of irony or scepticism: this is what they want to do and they will try their best to achieve it – anything is possible, “God willing”.

I am returning after an absence of several years and catching up with old friends like Solomon, who works in a private university. In many ways it all seems very familiar: the same donkeys and goats roaming the streets, the shoeshine boys, and people as friendly and chatty as ever.

However, the area of Addis where I am staying has changed a lot. There is a two-track railway being built down the middle of the main road; the central reservation that used to divide the two lanes of traffic that had some trees, some shrubs and a few men sleeping is gone. Many of the small family businesses, shops and restaurants have either been knocked down or closed down due to lack of business. All along the main road enormous buildings are being constructed and Solomon tells me that he is worried about the infrastructure needed to support them. Whether they become offices, colleges, hospital or shopping malls they will need additional electricity, internet connectivity, water supply and sewage but there is no evidence that these already over stretched services are going to be upgraded.

Meskel Square in the centre of Addis seems to have lost a lot of its glamour (if that’s the right word); the railway carves through the air, at eye-level with the stand where the leaders of the Derg used to stand to watch their military displays. The artificial palm trees with the flashing lights and the giant TV screen have gone. Now it seems to be a giant coach park.


I am off for a stroll through the evening warmth, the dust and the rubble. I will probably stop for a drink. A fresh squeezed mango juice? A freshly brewed macchiato? Can’t decide!