Friday, January 24, 2014

The Missing Faces of Ethiopia’s Poor

Yenenesh Yigsaw (right) recovers from her latest reconstructive surgery with other Noma patients at a recuperation centre outside of Addis Ababa, Ethiopia's capital. Credit: Nick Ashdown/IPS
Gelegay's affability is notable because of what he's gone through. The 34-year-old farmer from a village in Ethiopia's Gojam region is a survivor of Noma, a rare flesh-eating infection that rots away the face.
When he was just two years old, Gelegay noticed black spots forming on his nose, which quickly spread downwards to his mouth. He received rudimentary treatment, but the diseased part of his face fell off.
Noma is only found amongst children (primary incidence is between the ages of one and four) in the poorest regions of the world, such as rural parts of sub-Saharan Africa and India. The World Health Organisation estimates there are 140,000 new cases globally each year.

Tuesday, January 14, 2014

“አለሁ ---- አልሞትኩም”

ረቡዕ ማታ በዛሚ 90.7 ኤፍ ኤም ሬዲዮ ላይ “አርቲስት ፈለቀ አበበ አረፈ” በሚል በስህተት በተነበበ ዜና እረፍት  ምክንያት አርቲስቱ፣ ቤተሰቦቹ፣ጓደኞቹና አድናቂዎቹ እስከ ሀሙስ እለት ተረብሸው ነበር፡፡ በርካቶች ዜናውን ባለማመን ነገሩን ለማረጋገጥ አርቲስት ፈለቀ አበበ ተንቀሳቃሽ ስልክ ላይ ሲደውሉ ማምሸታቸውንና መዋላቸውን አርቲስቱ ገልጿል፡፡ በስህተት ከተሰራጨው ዜና እረፍት በኋላ አርቲስት ፈለቀ የማር ውሃ አበበ ስለተፈጠረበት ስሜትና አጠቃላይ ሁኔታ ከጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ ጋር  አጭር ቃለምልልስ አድርጓል፡፡

የሞትህን ዜና በምን ሁኔታ ሰማህ?

ረቡዕ ወደ ማታ ቤት ቁጭ ብዬ እየሰራሁ ሳለሁ፣ ባልተለመደ መልኩ ስልኮች በተከታታይ መደወል ጀመሩ፡፡ አስደንጋጭ ነበር፡፡ ብቻ የሆነ ነገር እንዳለ ያስታውቃል፡፡
ዜና እረፍትህን ሰምተው መደወላቸውን እንዴት አወቅህ?
አንዱን ጓደኛዬን በድፍረት ጠየቅሁት፡፡ ምክንያቱም በዚህ ፍጥነት በተከታታይ ሲደወል ለእኔ የተለመደ አይደለም፡፡  “ምንድን ነው ነገሩ? አካባቢው ላይ የተፈጠረ ነገር አለ እንዴ? ብዙ ሰው በተከታታይ እየደወለልኝ ነው” ብዬ ስጠይቅ፤“አይ ሞተሀል ተብሎ በሬዲዮ ተነግሮ ነው” ሲለኝ ክው ብዬ ደነገጥኩኝ፡፡ ደግሞ ያስታውቃል፤ አንዳንዶቹ ልክ ስልኬን አንስቼ “ሀሎ” ስላቸው ቶሎ ይዘጉታል። ብቻ መኖሬን ነው ማወቅ የሚፈልጉት፡፡ እንደዚህ ካደረጉት ውስጥ ጓደኛዬ አርቲስት ሰለሞን ቦጋለ አንዱ ነው፡፡ አማኑኤል መሀሪ እንዲሁም ቤተሰቦቼም ድምፄን ሰምተው ብቻ ስልክ ዘግተዋል፡፡ ምክንያቱም ወደ ቤተሰቦቼም ይደወል ነበር፡፡ ከውጭ አገር ሁሉ የስልክ ጋጋታው ሊያቆም አልቻለም፡፡

ሲደውሉልህ የሰዎች ስሜት እንዴት ነበር?

በጣም ህመም የሆነብኝ እሱ ነው፤ በጣም የሚያለቅሱና ኡኡ የሚሉ ነበሩ (ለቅሶ…) በጣም ያሳዝናሉ፤ እኔም አብሬያቸው አለቅስ ነበር (ረጅም ለቅሶ)…
ሬዲዮ ጣቢያው ጋ አልደወልክም ?
ትንሽ ቆይቶ--- ከዛሚ 90.7 ኤፍ ኤም ደወሉልኝ፡፡ “በስህተት ነው ፈለቀ አበበ ሞተ ያልነው፤ የሞተው ግን አርቲስት ፈለቀ ጣሴ ነው፤ አንተ በጣም ታዋቂ ስለሆንክ ፈለቀ ስንል አፋችን ላይ የገባው የአንተ አባት ስም ነው” አሉኝ፡፡ ነገር ግን ሰው በጣም ያለቅሳል፤ በጣም ያሳዝናል፡፡

ይቅርታ ጠየቁ ወይስ----

Monday, November 4, 2013

“ባህላዊውን ሙዚቃ ወጣቱ እንዲወደው እፈልጋለሁ” አበባየሁ ገበያው


አብዛኛው ሙዚቃ አፍቃሪ የሚያውቀውና ዝነኝነት የተቀዳጀበት ዘፈኑ “ሰላ በይልኝ” የሚለው ቢሆንም በኢትዮጵያ ያልተለቀቁ በርካታ ዘፈኖች ያህል እንዳሉት ይናገራል - ወጣት ድምፃዊ ጐሳዬ ቀለሙ (ጃኪ ጎሲ)፡፡ ወደ ሙዚቃው ህይወት የገባው ገና በ13 ዓመቱ ነበር - በትያትር በኩል፡፡ በታዳጊነቱ ከታዋቂ አርቲስቶች ጋር ትያትር ለማሳየት ወደ ፈረንሳይ ሄዶ ለበርካታ ዓመታት ወደ አገሩ አልተመለሰም፡፡ በጀርመን በሬጌ ባንድ ውስጥ እንግሊዝኛ ዘፈኖችን ሲያቀነቅን የቆየው ጃኪ ጐሲ፤ የመጀመርያ የአማርኛ ነጠላ ዜማውን ኢትዮጵያ መጥቶ እንደሰራ ይናገራል፡፡ ባህላዊ ዘፈኖችን እያዘመነ በመስራት ወጣቱ ባህላዊውን ሙዚቃ እንዲወደው የማድረግ ፍላጐት አለው፡፡ 
በአሁኑ ሰዓት በአዲስ አበባ የመጀመርያ ሙሉ አልበሙን ለማውጣት ተፍ ተፍ የሚለው ጃኪ፤ ከአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አበባየሁ ገበያው ጋር በህይወቱና በሙዚቃ ሙያው ዙሪያ እንዲህ አውግተዋል፡-
ሥራ ላይ ነው እንዴ ያደርከው? የደከመህ ትመስላለህ ?
አዎ ፤አልበም እየሰራሁ ነው፡፡ ሙሉ አልበም የማወጣው ለመጀመሪያ ጊዜ ስለሆነ ጥሩ ስራ ለመስራት ቀን ከሌት እየተጋሁ ነው፡፡ 
ምን ዓይነት ዘፋኝ ነኝ ብለህ ነው የምታስበው? ባህላዊ ወይስ ዘመናዊ ?
አቅሜ ብዙ ነው ብዬ ነው የማስበው። ባህላዊውንም ዘመናዊንም እችላለሁ። ባህላዊ ሙዚቃን ሞደርን ለማድረግ ነው የምፈልገው፤የባህሉን ሙዚቃ ወጣቱ ትውልድ እንዲወደው እፈልጋለሁ፡፡ ባህሌን ስለምወድ ነው ወደ ባህላዊው የመጣሁት፡፡ ውጭ አገር ሬጌ ባንድ ውስጥ እንግሊዝኛ ሙዚቃ ነበር የምጫወተው፡፡ ያ ደግሞ እኔን አይገልፀኝም፤ እኔነቴን አይወክልም ብዬ ስለማምን ነው የተውኩት፡፡ በዘመናዊ ሙዚቃ ውስጥም አለሁኝ፡፡ ባህላዊ ዘፋኝ ብቻ አይደለሁም። በአዲሱ አልበሜ ባህላዊ ዘፈን ብቻ አይደለም ይዤ የምቀርበው፤አቅሜንም ለማሳየት ስለምፈልግ ለአድናቂዎቼ የተለያዩ ነገሮች ነው የማቀርበው፡፡ ኢትዮጵዊ ቀለም ያላቸው ዘመናዊ ዘፈኖችን ነው የሰራሁት፡፡

Sunday, November 3, 2013

ስብሐት ገ/ እግዚአብሔር ስንት አይነት ገጸ-ባህሪ ነው


ከበፍቃዱ አባይ

አመቱ ምንም እንኳን 2005 ዓ.ም ላይ ቢሆንም በቅርቡ ልንለው በምንችለው መልኩ ላንባብያን የደረሰውንና ስብሐት ገ/እግዚእብሔርን የተመለከተውን መጽሐፍ አነበብኩት፡፡ስለመጽሕፉና በውስጡ ስለተካተቱ የተለያዩ መልከ-ስብሐት ሐሳቦችን አስመልከቶም በተለያዩ የህትመት ውጤቶች ላይ የቀረቡ ክርክሮችንም ሳነብ ቆይቻለሁ፡፡ በመጽሐፉ ላይ ከተካተቱት የስብሐት መልኮች ውስጥ ግዝፍ ነስቶ የበርካታ አንባብያንን ቀልብ ለመሳብ የቻለው የአርክቴክቱ ሚካኤል ሽፍራው ስብሐትን ከሌላ ማዕዘን የተሰኘው እይታ ነው ለማለት ይቻላል፡፡ በዚህ ሐሳብ ዙሪያ ታድያ የቀረቡት በርካታ ክርክሮችም ውሐ የሚያነሱ ሆነው አግኝቻቸዋለሁ፡፡ እኔም ስለ መልክአ-ስብሐት ያለኝን አተያይ ለመከተብ ጊዜ ያላጠፋሁ ቢሆንም ለአደባባይ መብቃቱ ላይ ግን ሰንፌ ቆይቻለሁ ዛሬም ሰዓቱ ባለመርፈዱ ስለ መጽሐፉ ጥቂት ለማለት ወድጃለሁ፡፡
መልክዐ ሰብሐት የሚል ስያሜ ያለው ይህ መጽሐፍ በ30 ጸሐፍት፤ደራስያንና ሰዓሊያን እንደተጻፈ የጀርባ ሽፋኑ ላይ የተገለጠ ቢሆንም እኔ ግን በቆጠራ የደረስኩበት 27 ባለሙያዎች የተሳለፉበት መሆኑን ነው፡፡ያም ሆነ ይህ ግን ስበሐት በሐገራችን ካሉ በጣት ከሚቆጠሩ ስመ ጥር ደረስያን/ት/መሐከል እጅግ እድለኛውና በተለያዩ ጸሀፍት ሊዘክር የበቃ ደራሲና ተርጓሚ ነው ለማለት እችላለሁ፡፡በህይወት በነበረበት ወቅት በተለያዩ ወጣቶች ልደቶቹ የተከበሩለት፤በታላላቅ መደረኮች ለመታደም የቻለ፤ከህልፈቱም በኋላም ሆነ በፊት በስሙ ጥቂት የማይባሉ ስነ-ጽሑፋዊ በረከቶች የተለገሱለት ኢትዮጽያዊ ነው፡፡ሰሞነኛው መልክአ ሰብሐትም አንግዲህ የዚህ የሰውየው ስም መነሻ ለመሆን የበቃ መጽሐፍ ነው፡፡ለስብሐት ከፍ ያለ ፍቅርና አክብሮት ያላቸው ጸሐፍት፤ገጣምያንና ሰዓሊያን የታደሙበት መጽሐፍ ታድያ በአብዛኛው ወደ መወድስ ስብሐት ያደሉ ናቸው ለማለት ይቻላል፡፡ጸሐፍቱ ለስብሐት ያላቸውን ክብርና ፍቅር ለመግለጽም የክብር ዶክትሬት የሚገባው ስለመሆኑም ጭምር በስራዎቻቸው ላይ ወትውተዋል፡፡ ከዳኛቸው ወርቁ እስከ ሲግመንድ ፍሩድና ቻርልስ በግዴይር፤ከሄሚንጉዌ አስከ ሆቺሚኒ ደረስ ስማቸው በተወሳበት በዚህ መጽሐፍ ላይ የተለያዩ ሐሳቦች ሰፍረዋል፡፡ከዚህ በተለየ መልኩ የስብሐትን መልክ ፍጹም በማጠየምና በድፍረት ሌላ የተጠየቃዊ ሐሳበ ትንታኔ ይዞ ለመምጣት የደፈረው አርክቴክቱ ሚካኤል ሽፈራው ብቻ ነው፡፡ይህ የሚካኤል ስራ መኖርም ነው የመጽሐፉን ርዕስ ሙሉ ይሆን ዘንድ ያስቻለው፡፡እንደሌሎቹ የስብሐት መልክ ገለጻ ቢሆን ኖሮ የመጽሐፉ ርዕስ ከመልከአ ስብሐት ይልቅ ለመወድሰ ሰብሐት የቀረበ ይሆን ነበር፡፡ይህ መጽሐፍ ሰሞኑንም በጣይቱ ሆቴል ጃዝ አምባ ላውንጅ በርካታ የስብሐት አድናቂዎችና የአርታኢው አለማየሁ ገላጋይ ተጠረዎች በታደሙበት ተመርቋል፡፡በዕለቱም ከቱባ የስነ-ጽሁፍ ሰዎች እስከ ወጣቶቹ ጭምር በመድረኩ ላይ ስለ መልክአ ሰብሀት መጽሀፍ ምረቃ ሲሉ ስለ ስብአት ለአብ የተለያዩ ስራዎቻቸውን አቅርበዋል፡፡49 የኢትዮጽያ ብር የተተመነለትንና 277 ገጾችን በጉያው የሸከፈውን መልክአ ስብሀት ብዙዎች እንደሚያነቡት ተስፋ አድርጋለሁ፡፡
ከንባባችን በመለስም መጽሀፉን አንብበን ስናበቃ የምንነጋገርባቸው የሐሳብ ሰበዞችን ማቀበሉ እንደማይቀርም እገምታለሁ፡፡ይህንን መንደርደሪያ ምርኩዝ በማድረግም መጽሐፉ ለገበያ መቅረቡ በፊትም ሆነ ከረበ በኋላ ስብሐት ገ/እግዚአብሔርን አስምልከቶ ለራሴ ስጥይቃቸው የነበሩ ጥያቄዎቼን ይበልጥ ያቀጣጠሉ መግፍኤ ሐሳቦችን አነሳ ዘንድ አነሆ አልኩ፡፡
ግለ-ምልከታ

Friday, November 1, 2013

The greatest athletes of all time appear together in a short film about Ethiopian running.


Shot in Adis Ababa, Haile Gebrselassie, Kenenisa Bekele, Tirunesh Dibaba and Meseret Defar tell the story of distance running in Ethiopia. Talking ahead of this year's Bupa Great North Run, the athletes explain what it means to win a gold medal in Ethiopia, and what it takes to be the best in the world.

Haile Gebrselassie is a two time Olympic Gold Medallist, winning the 10,000m at the Atlanta and Sydney Olympic Games. Kenenisa Bekele won the Olympic 10,000m in Athens and Beijing, where he also won the 5,000m. Meseret Defar won the 2004 and 2012 Olympic 5000m titles, and Tirunesh Dibaba won the 5,000 and 10,000m at the Beijing Games and the 10,000 at London 2012. Between them they have broken dozens of World Records, and taken dozens of World Titles on the track and country.

Tuesday, September 3, 2013

Africa


POPULATION
* Africa’s population hit the 1 billion mark in 2010, with annual growth rates at 2.0 percent and 1.6 percent in Northern and Southern Africa, respectively, 2.5 percent and 2.7 percent in Western and Middle Africa, respectively, and the African average at about 2.4 per cent.
* Africans are expected to number 2 billion by 2050.
* Africa has the second highest population after Asia.
* Africa accounts for 14 percent of the world’s population.
* There are more than 200 million youth in Africa, comprising more than 20 percent of the continent’s population.
* Close to 70 percent of Africa's population is aged below 25, making it the youngest continent in the world. For example, in Kenya, young people are close to 75 percent of the population.
* Uganda has the youngest population in the world, with a fertility rate of 6.2 children.
* Rates of urbanization in Africa are the highest in the world. By 2020, 66 percent of the continent’s population are expected to live in cities and be of working age.
* Poverty levels of Africa’s population are expected to decline to 20 percent by 2020, from around 43 percent in 1995.
* Africa presents the highest proportion of illiterate youth in the world, estimated at about 25 percent, according to the African Developmetn Bank's 2013 Economic Outlook.  Estimates suggest that about 133 million young people, accounting for over 50 percent of the youth population in Africa, lack formal education.
* About five million graduates are produced annually by African universities.