Monday, February 2, 2015

‹‹ልጅነቴ በሙዚቃ ተጣጥሞ አልፏል›› ፀሐይ ዮሐንስ

 ተጻፈ በ  
የፀሐይ ዮሐንስ
 ‹‹ማንበብና መጻፍ ዋናው ቁም ነገር፤ ከሕይወቴ ጐሎ እሸበር ጀመር›› የሚለው ስንኝ የብዙዎች ትዝታ ነው፡፡
በጊዜው በመሠረተ ትምህርት ዘመቻ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደነበረውም ይታመናል፡፡ ‹‹ሳብ ሳም››፣ ‹‹ተባለ እንዴ›› እና ‹‹ያላንቺማ›› የፀሐዬ (ብዙዎች እንደሚጠሩት) ስም ከሚነሳባቸው ዘፈኖች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ በተመሳሳይ ስለ ሀገር ያዜማቸውም የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ ፀሐዬ ‹‹የኔታ›› የተሰኘ አልበም በቅርቡ ለቋል፡፡ አልበሙንና አጠቃላይ የሙዚቃ ሕይወቱን በሚመለከትምሕረተሥላሴ መኰንን ከፀሐዬ ዮሐንስ ጋር ቆይታ አድርጋለች፡፡  
ሪፖርተር፡- ከመታወቅህ አስቀድሞ የሙዚቃ ሕይወትህ ምን ይመስል ነበር?
ፀሐይ፡- ጃንሜዳ አካባቢ መኖሬ ወደ ሙዚቃ ለመግባቴ ትልቁ ምክንያት ይመስለኛል፡፡ የልጅነቴን ተሰጥኦ እዛ ነው ያዳበርኩት፡፡ በምንነጋገርበት በዚህ የጥምቀት ሰሞን ብዙ ትዝታ አለኝ፡፡ ጥምቀት ለሙዚቃ ፍቅሬ መንገድ የከፈተ ነው፡፡ ያደግኩበትም ግቢ ጃንሜዳ አጠገብ ባለው ሙዚቀኛ ግቢ ነው፡፡ ጥላሁን፣ መሐሙድና ብዙነሽ የነበሩበት ክብር ዘበኛ ኦርኬስትራ ትልቁን ሚና ተጫውቷል፡፡ ጠዋት ደብተር ይዤ ሄጄ እዛ እውላለሁ፡፡ ክብር ዘበኛ ባልሠራም የክብር ዘበኛ ልጅ ስለሆንኩኝ ልጅነቴ በሙዚቃ ተጣጥሞ አልፏል፡፡ 
ሪፖርተር፡- ድምፃዊነትን ሙያዬ ብለህ ‹‹በርታ ዘመዴ››ን ከተጫወትክ በኋላስ? 
ፀሐይ፡- ያኔ ዜማ ማውጣት ጀመርኩ፡፡ ‹‹ማንበብና መጻፍ›› የኔ ዜማ ነው፡፡ አቶ ተስፋዬ ለማ አምባሳደር ቴአትርን ባቋቋሙበት ጊዜ በ1970 ዓ.ም. ከጓደኞቼ ጋር የመጀመሪያ ቅጥሬን አምባሳደር አደረግኩ፡፡ ከዛ በፊት ከክብር ዘበኛ ጋር ለዕድገት በኅብረት ዘመቻ ‹‹በርታ ዘመዴ ዘማቹ ጓዴ››ን ከሒሩት በቀለ ልጅ ጋር ሆነን ሠርተናል፡፡ ከዛ በኋላ አሻራዬ ያረፈባቸው 14 አልበሞች አሉኝ፡፡ 
ሪፖርተር፡- የመጀመሪያ አልበምህ እንዴት ነበር? 
ፀሐይ፡- ሙዚቃ ቤቶች ፕሮዲውስ ያደርጉ ስለነበር ልምድ ያለው ሰው ይፈልጋሉ፡፡ በዛ ወቅት ገና ልጅ ነኝ፡፡ ስሜት እንጂ ልምድ የለኝም፤ ስሜቴን ወደ ተግባር ለመቀየር ገንዘብ ስለሚያስወጣ ፕሮዲውሰሩ ይቸገራል፡፡ እንደ ምንም የመጀመሪያው ካሴት በሱፐር ሶኒክ ሙዚቃ ቤት አሳታሚነት ተሠራ፡፡ ጥሩ እየተሸጠ እያለ በአጋጣሚ እነ መሐሙድ አህመድና ውብሸት ፍስሐ ወደ ኤሜሪካ ከዋልያስ ባንድ ጋር ሄደው በኤሌክትሮኒክስ መሣሪያ ታጅበው ‹‹ማለዳ ማለዳ›› ያለበትን ካሴት አወጡ፡፡ ካሴቱ የእኔን ሸፈነውና ብዙ ሳይደመጥ አለፈ፡፡ በዓመቱ በንዴት ‹‹ፍንጭቷ››ን ሠራሁ፡፡ ‹‹ፍንጭቷ››ን ይዤ ስወጣ ፀሐዬ ዮሐንስ የሚለው ስምም ተገኘ፡፡ 
ሪፖርተር፡- ትንሹና ከፍተኛውስ ክፍያ ስንት ነው? 
ፀሐይ፡- ያልተለመደ ዘዬና ድምፅ ይዤ ስለመጣሁ በሽያጭ ‹‹ፍንጭቷ›› በጣም ኃይለኛ ነበር፡፡ ‹‹ሳብ ሳም››፣ ‹‹ተባለ እንዴ›› እና ‹‹ያላንቺማ›› በጣም ጥሩ ሥራዎች ነበሩ፡፡ የመጀመሪያ ክፍያዬ 3,000 ብር ነበር፡፡ እንደ ጀማሪና በወቅቱ ገንዘቡ ከነበረው ዋጋ አንፃር ትልቅ ነበር፡፡ የ300,000 ሺሕ ብር ያህል አቅም ነበረው፡፡ የመጀመሪያ ካሴት ስም ማግኛ ስለሆነ ከክፍያ ይልቅ ስም ማግኘቱ ላይ አተኩሬ ነበር፡፡ 
ጥበብን በገንዘብ መለካት አስቸጋሪ ነው፡፡ በተለይ በእኛ ሀገር በሥራውና በተሸጠው መጠን አይከፈልም፡፡ መልካም ሥራ በመሥራት መልካም ስም ነው የሚተርፈው፡፡ በ‹‹ተባለ እንዴ›› ጊዜ ክፍያው 100,000 ሺሕ ብርም ደርሶ ነበር፡፡ ከ‹‹ተባለ እንዴ›› በኋላ የካሴት ሥራ የተበላሸበት ዘመን ነው፡፡ ሰው ሸጦ የሚያተርፍበት ጊዜ አልነበረም፡፡ ኮምፒዩተር መጣና በደቂቃ ሁሉም ሰው የሚቀዳበት ደረጃ ደረሰ፡፡ ሲዲ ከመምጣቱ በፊት ሽያጭ ጥሩ ነበር፤ ከፍተኛ የገቢ ምንጭም ነበር፡፡ ኦሪጅናል ካሴት 13 ብር ይሸጥ ነበር፡፡ ለማባዛት ባዶ ካሴት አምስት ብር ማስቀጃ ሦስት ብር ነበር፡፡ አምስት ብር ጨምሮ ኦሪጅናል መግዛት ስለሚመረጥ ገበያ ነበር፡፡ ዛሬ በአንድ ፍላሽ እስከ 500 ዘፈን ስለሚያዝ ኦሪጅናል የሚገዛ የለም፡፡ አቁሞ የሚያስኬደን ከኮንሰርት የሚገኝ ገንዘብ ነው እንጂ ዛሬ የሚሠራው ለነገ አያበረታታም፡፡ ጥበቡ እየሞተ ይመስለኛል፡፡ ባወጣሁት ልክ ካላገኘሁ የመሥራት አቅሜ ይዳከማል፡፡ ዛሬ እኔ ነገ ደግሞ ሌላው ከዘርፉ ይወጣል፡፡ በ‹‹የኔታ›› አልበም ብዙ ነው ያወጣሁት፡፡ የሚመጣውና የሚገኘው ተመጣጣኝ ካልሆነ ነገ ለጥበብ ብዬ ለፍቼ ልሠራ አልችልም፡፡ አልበሙ በሙሉ ባንድ ነው የተሠራው

Friday, January 30, 2015

The State of Art in Ethiopia



የታላቁ ሜትር አርቲስት የአለም ሎርየት አፈወርቅ ተክሌ መሳጭ ንግግር በኮንግርስ  አፍ ላይብረሪ


Renowned artist Afewerk Tekle presented a lecture on the state of art in his native Ethiopia.Speaker Biography: Afewerk Tekle was one of Ethiopia's most celebrated artists, particularly known for his paintings on African and Christian.

Atse Tewodros from Atse Tewodros Project


Gabriella Ghermandi

"I will risk having my bones be shattered
I will risk having my blood flow from my body like a sea
I am willing to lose my life rather than yield an inch of my
country’s independence …
… I will fight those who have come cloaking their intentions in the
Gospel, to subjugate our land"

"Atse Tewodros", is the third track of the "Atse Tewodros Project" CD,
dedicated by Gabriella Ghermandi to Emperor Tewodros II "who
modernized Ethiopia while respecting traditions"; one of the most
beloved emperors in Ethiopian history, He was the first emperor who was not of Ethiopian royal descent. He rose to power because of his perseverance and charisma, qualities that charmed the Ethiopian people to the point that they broke with centuries-old tradition and supported his accession to the throne. He was also the emperor who fought against Queen Victoria’s army and defended Ethiopian independence in the century of African colonization.
A mix of tradition and modernity, dressed with Ethiopian pride, the CD
includes also some Shellela (war songs) as a tribute to the Arbegnoch,
the Ethiopian patriots that fought the Italian invasion between 1935
and 1941.

The project, fully independent and self financed, started in 2010 in
Addis Ababa, as a result of a collaboration among Gabriella Ghermandi,
the Ethiopian composer Aklilu Zewdy and Professor Berhanu Gezaw. It
immediately caught the interest of Michele Giuliani, an Italian
pianist and composer who is the leader of the Reunion Platz Jazz Trio.

After a successful foundraising that collected over hundreds of
donations from individuals and associations, Gabriella Ghermandi and
the Reunion Platz Trio flown to Addis and met traditional Ethiopian
musicians of the Ethiocolor Band (official group of 2014 WomaX
edition) and to complete the musical arrangements and record the CD
(in live sessions at Langano Studio, engineered by Abegasu Shiota).

Though not distributed yet, the CD already got positive reviews from
Italian and international press. This is and excerpt from fRoots: "The
music is clear, thoughtful and unforced. The contrast between
Gabriella’s warm, accurate voice and washint (flute) and dry, aching
krar (lyre) and calm, jazzy rhythm section is powerfully evocative.
Worth seek- ing out – and you will have to seek it out, being a
self-published album at present, though a label to take it up must be
likely".
http://www.worldmusic.net 

Monday, September 15, 2014

የእንቁጣጣሽ ስጦታ! “ክላሲካል ሙዚቃን በልምድ መጫወት አይቻልም”

  አዲስ አድማስ

የኒውዮርክ ታይምስ መጽሔት “From Chopin to Ethiopia and Part way Back Again (“ከቾፐን እስከ ኢትዮጵያ እና ደርሶ መልስ”) በሚል ባስነበበው የሙዚቃ ቅኝት ስቲቭ ስሚዝ ስለግርማ ይፍራሸዋ ያሰፈረው በከፊል ይሄን ይመስላል፡-
 “…በተነፃፃሪ ሲታይ፤ ስለክላሲካል ሙዚቃ በአፍሪካ፤ የሚያመላክቱ ጥቂት ማረጋገጫዎች ብቻ ይኑሩ እንጂ የምዕራቡ ክላሲካል ባህል በሌላው ዓለም ማለትም ከቬኔዝዌላ እስከ ቻይና እንደተንሰራፋው ሁሉ የአፍሪካንም ዙሪያ መለስ ማዳረሱ ገሀድ ነው፡፡ ለዚህ አስረጅ የሚሆነን 45 ዓመቱ ኢትዮጵያዊ ፒያኒስትና ቀማሪ ግርማ ይፍራሸዋ በብሩክሉንኢሹ ፕሮጀክት ሩምቅዳሜ ምሽት ያቀረበው ምርጥ የፒያኖ ሥራ፤ እጅግ ብርቅ፣ ሥነ ውበታዊና ተምሳሌታዊ የክላሲካል ሙዚቃ መናኸሪያ መሆኑን የሚያሳይ ነው!
…. ግርማየኢትዮጵያዊያን በገናሊባል በሚችለው በክራር ነው የሙዚቃ ልጅነቱን የጀመረው፡፡ አዲስ አበባ ሙዚቃ /ቤት ሲገባ ከፒያኖ ጋር ተገናኘ፡፡ ከዚያ ነው በነቃ አዕምሮው በቡልጋሪያ የሶፊያ ስቴት ኮንሰርቫቶሪ መደበኛ ትምህርቱን ገፍቶ የተካነው
“… ወደ ኢትዮጵያ 1995 .. ከተመለሰ በኋላ ግርማ ደረጃውን የጠበቀ ክላሲካል ትርዒት ምን እንደሚመስል ደርዝ ያለው ግንዛቤ ማስጨበጥን ሥራዬ ብሎ ከመያያዙ ሌላ፤ አዳዲስ የሙዚቃ ስራዎችን ፅፏል፡፡ ለነዚህ አዳዲስ የጥበብ ስራዎች መቀመሪያ ይሆነው ዘንድ የአውሮፓን የጥበብ መላ ከኢትዮጵያ ሙዚቃና ሥነ-ትውፊታዊ ዕሴት ጋር በማጋባት ተጠቅሟል፡፡....››


ከፍተኛ ሽያጭ ያስመዘገበው አዲሱ አልበሙ በአሜሪካ በቢልቦርድ ሰንጠረዥ 23 ደረጃ አግኝቷል ታዋቂው ፒያኒስት ግርማ ይፍራሸዋ በቅርቡ በአሜሪካ ያስመረቀው “Love and peace” የተሰኘ አዲስ አልበሙ፤ በቢልቦርድ ሰንጠረዥ 23 ደረጃ ላይ እንደተቀመጠለት ይናገራል፡፡ በአሜሪካ ያቀረበው ኮንሰርት እንደተወደደለት የገለፀው ፒያኒስቱ፤ ኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ በአድናቆት የተሞላ ጽሑፍ እንዳወጣለት ጠቁሟል፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ኤልሳቤት ዕቁባይ ከግርማ ይፍራሸዋ ጋር ያደረገችው ቃለምልልስ እንዲህ ቀርቧል፡፡ ወደ ሙዚቃ እንዴት እንደገባ በመናገር ይጀምራል፡-


ሙዚቃ የጀመርኩት በልጅነቴ ክራር በመጫወት ነው፡፡ ክራር ስጫወት ነው ያደግሁት፡፡ ፡፡ሙዚቃን በሳይንሳዊ መንገድ ለማጥናት ደግሞ  ያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት በመግባት፤ ከባህል ክራር፣ ከዘመናዊ ደግሞ ፒያኖን ለአራት አመት ተማርኩ፡፡ የያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት ትምህርቴን እንዳጠናቀቅሁ፣  1980 ስኮላርሺፕ አግኝቼ ወደ ቡልጋሪያ  አቀናሁ፡፡
እዚያ ከሄድክ በኋላ ግን ችግር ገጠመህ

Monday, August 18, 2014

የጳውሎስ መልእክት ወደ ኢትዮጵያ ሰዎች !

ርዕስ- ጳውሎስ ኞኞ (1926-1984)፣
የገፅ ብዛት - ከፎቶና ማጣቀሻ ጽሑፎች ዝርዝር ጋር 308፣
የሽፋን ዋጋ - 84 ብር (24 ዶላር)፣
የህትመት ዘመን - 2006 ዓ.ም
ህትመት - አርቲስቲክ ማተሚያ ድርጅት
ጸሐፊ - ደረጀ ትዕዛዙ

በዘመናችን ግለታሪኮችና ታሪኮች በብዛት ባይሆንም በተሻለ መጠን ለህትመት እየበቁ ናቸው፣ ይህ መልካም ጅምር መጠናከር ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም ዓለማችንን የቀየሩዋት ባለ ልዩ አዕምሮ ግለሰቦች ናቸው፤ በእነሱ ጥረትና የድካም ፍሬ ድምሩ ህዝብ ተጠቃሚ ሆኗል፤ ይሆናልም፡፡ እንኳንስ ተፈጥሮ አድልታ ባለ ምጡቅ አዕምሮ ያደረገቻቸው ግለሰቦች ይቅሩና የኔቢጤው በረንዳ አዳሪ ሁሉ ቀርቦ የሚያነበው ቢያገኝ ታላቅ መጽሐፍ ነው፤ ታላቅ መረጃ በውስጡ ይኖራል፡፡
ከነገስታትና ልኡላን ዜና መዋዕሎች በቀር እብዛም ያልተለመደ የነበረው የግለሰቦች ታሪክ በቤተሰቦቻቸው፣ ወይም መልካም ፈቃዱና ችሎታው ባላቸው ግለሰቦች አማካይነት እየተጻፈ ልምዳቸውን እንድንካፈል የላቀ ድርሻ እየተወጡ ናቸው፡፡ በቅርቡ ታትሞ ገበያ ላይ የዋለውና በጳውሎስ ኞኞ የህይወትና ሥራ ታሪክ ላይ የሚያጠነጥነው መጽሐፍም ከእነዚህ የግለሰብ ታሪኮች የሚመደብ ነው፡፡
በዘጠኝ ምዕራፎች የተከፋፈለው የ“ጳውሎስ ኞኞ” መጽሐፍ፤ የተለያዩ ፎቶግራፎችንና ውሱን ሰነዶችንም አካትቷል፡፡ ስለጳውሎስ ልደት፣ ዕድገት፣ ትምህርት፣ ሥራና ባህርይ የሚያትተው ይህ መፅሀፍ፤ ከጳውሎስ ጋር ባላንጣ ስለነበሩት የወቅቱ የማስታወቂያ ሚኒስትር ደጃዝማች ግርማቸው ተክለሐዋርያትም የሚያካፍለን ቁም ነገር አለ፡፡
ጳውሎስ ያልሞከረው ሥራ የለም ማለት ይቻላል፤ ግለሰብ ሱቅ ውስጥ ተቀጥሮ መስራት የጀመረው ገና በልጅነት ዕድሜው ሲሆን ትምህርቱን ከአራተኛ ክፍል ያቋረጠውም በድህነት ምክንያት ነው፡፡ (ገፅ 16) ከግሪካዊው ኞኞ እና ከኢትዮጵያዊቷ ወ/ሮ ትበልጫለሽ ቁልቢ ገብርኤል አካባቢ የተወለደው ጳውሎስ፤ የልጅነት ህይወቱ የተመሰቃቀለ ነበር፡፡ እናቱ ፍጹም ድሃ በመሆናቸው እንደ እመጫት ድመት በየቦታው ይዘውት ስለሚዞሩ በትምህርቱ ላይ ጫና መፈጠሩ የግድ ነበር፡፡

Wednesday, June 18, 2014

ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ኢስተር ራዳ ከአመቱ 50 የዓለማችን ተጽዕኖ ፈጣሪ አይሁዳውያን አንዷ ሆነች

አዲስ አድማስ

የእስራኤል ፕሬዚዳንት፣ ጠ/ሚንስትር፣ የገንዘብ ሚ/ር እና የኢኮኖሚ ሚ/ር በዝርዝሩ ውስጥ ተካተዋል
ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ታዋቂ ድምጻዊት ኢስተር ራዳ፣ ‘ዘ ጀሩሳሌም ፖስት’ ጋዜጣ የአመቱ የዓለማችን ተጽዕኖ ፈጣሪ አይሁዳውያን ብሎ ከመረጣቸው 50 ታዋቂ ግለሰቦች መካከል አንዷ ሆነች፡፡


  በሶል፣በአር ኤንድ ቢ እና በፋንክ ስልቶች የተቃኙና የኢትዮ-ጃዝ ቃና ያላቸው ሙዚቃዎችን የምትጫወተውና “የእስራኤል የሶል ሙዚቃ ንግስት” በመባል የምትጠራዋ ኢስተር ራዳ፣ በእስራኤል ብቻም ሳይሆን በመላ አለም በርካታ አድናቂዎችን ማፍራት የቻለች ድምጻዊት መሆኗን ‘ዘ ጀሩሳሌም ፖስት’ ባለፈው ሰኞ ይፋ ባደረገው መረጃ መስክሮላታል፡፡
ጋዜጣው ተስፋ ከሚጣልባቸውና ከፍተኛ ስኬት ካስመዘገቡ የዘመኑ ተጠቃሽ ቤተ እስራኤላውያን አርቲስቶች ተርታ ትሰለፋለች ያላት ይህቺ ድምጻዊት፣ በተለያዩ ጊዜያት በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ ስኬታማ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን ማቅረቧንና፣ ኢትዮጵያዊ ቅኝት ያላቸውን ሙዚቃዎች እንደምትጫወትም ገልጧል፡፡
በሙዚቃው ዘርፍ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ማፍራትና ለኤምቲቪ አውሮፓ የሙዚቃ ሽልማት እስከመታጨት የደረሰችው ኢስተር ራዳ፣ ‘ኪሮት’ እና ‘ስቲል ዎኪንግ’ን በመሳሰሉ ፊልሞች፣ ሙዚቃዊ ቲያትሮችና ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማዎች ላይ በተዋናይነት በመስራት ድንቅ የትወና ክህሎቷን አስመስክራለች፡፡
በተለያዩ የአለም ክፍሎች የሚኖሩ ፖለቲከኞች፣ ተመራማሪዎች፣ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች፣ ስራ ፈጣሪዎች፣ ቢሊየነሮች፣ አርቲስቶችና በሌሎች ሙያዎች ላይ ተሰማርተው ውጤታማ መሆን የቻሉ ግለሰቦችን በዘንድሮው የአመቱ 50 የአለማችን ተጽዕኖ ፈጣሪ አይሁዳውያን ዝርዝር ውስጥ ያካተተው ዘ ጀሩሳሌም ፖስት፤ ከእነዚህም ውስጥ ኢስተር ራዳን ጨምሮ 15 ያህሉ ሴቶች መሆናቸውን ይፋ አድርጓል፡፡
ካቻምና በእስራኤል ጠ/ሚንስትር ቤኒያሚን ኔታኒያሁ፣ አምና ደግሞ በገንዘብ ሚንስትሩ የር ላፒድ ተይዞ የነበረውን የዚህ  ዝርዝር መሪነት፣ ዘንድሮ የአሜሪካ ትሬዠሪ ጸሃፊ የሆኑት ጃክ ሊው ተረክበውታል፡፡ በአገሪቱ ኢኮኖሚ ውስጥ ቁልፍ ሚናን በሚጫወተው በዚህ ዘርፍ ውስጥ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ የሚገኙት እኒህ ሰው፣ በፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ አስተዳደር ውስጥ ተጽዕኖ መፍጠር የቻሉ ተሰሚ ሰው እንደሆኑ ጋዜጣው ዘግቧል፡፡
በተጽዕኖ ፈጣሪነት ሁለተኛውን ደረጃ የያዙት አሜሪካዊቷ ቤተ እስራኤላዊ ጃኔት የለን ሲሆኑ፣ የአሜሪካን ተቀማጭ ገንዘብ ተቋም እንዲመሩ በመመረጥ በአገሪቱ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት ናቸው፡፡ እሳቸውን ተከትለው በዝርዝሩ የተካተቱት፣ ቤኒያሚን ኔታኒያሁ (የእስራኤል ጠ/ሚንስትር) እና ሽሞን ፔሬዝ (የእስራኤል ፕሬዚዳንት) ናቸው፡፡
አቪግዶር ሊበርማን (የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር)፣ የር ላፒድ (የእስራኤል የገንዘብ ሚንስትር) እና ናፋታሊ ቤኔትም (የእስራኤል የኢኮኖሚ ሚንስትር)፣ በዘንድሮው ተጽዕኖ ፈጣሪ ቤተ እስራኤላውያን ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱ ታዋቂና በአለም አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ መፍጠር የቻሉ ግለሰቦች መካከል ይጠቀሳሉ፡፡

 http://www.addisadmassnews.com

Wednesday, April 2, 2014

ያ 'ትውልድ ይደገም



ጥጥ ነድፎ በደጋን አሸከርክሮ ፈትሎ
ማግ ሰርቶ ልቃቂት በእንዝርት ጠቅልሎ
ድሩን ወደ ሸማ በመቃ አስማምቶ
ከወትት የነጣ ጋቢ ኩታ ሰርቶ
ጥበብ ያለበሰኝ በወግ በመዕረግ
ይደገም ያ ትውልድ ይተካ ይመንደግ።

ኤዱዋርዶ