Tuesday, August 18, 2015

ዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ ከተናገሯቸው ታሪካዊ ንግግሮች በጥቂቱ !

ዛሬ በማህበራዊ ድረገጽ  ከተቀባበልናቸው ነገሮች ታሪካዊ ቀንነቱን በመንተረራስ ዳግማዊ አጤ ምኒልክና (እምዩ ምኒልክ)
እቴጌ ጣይቱ (ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ) የተወለዱብት ቀን ዝክርን  ነው ፡፡

እኔም ካየሁት ላካፍላችሁ



- ሰው ሁሉ እኩል ስለሆነ ማንም ሰው ሰውን ባሪያ አይበል ።
- ሁሉም ሰው በየኃይማኖቱ ይደር ።

-
ድኻ እወደደበት ቦታ ይቀመጥ በዘር በወገን ልዩነት አይከልከል

-
የመሬት ጥያቄ ላቀረቡ የውጭ አገር ሰዎች ንጉሡ የሰጡት መልስ፡- ‹‹ የኛ አገር ፍትሐ ነገሥት ልዑሎች መሬት ይሽጡ አይልም ያገሬ መሬት ባለቤቱ ሌላ ነው ከአባቶቻቸው እየተቀበሉ ያቆዩት መሬት ነው ... መሬቱ የሁሉም ስለሆነ አይሸጥም ማንም ሰው መሬቱን ሊሸጥ አይችልም መሬትን መሸጥ፣ መስጠትም የሚችለው የመሬቱ ጌታ ነው ››

-
ለመንግሥት ተሿሚዎች የሰጡት መመሪያ፡- ‹‹… እንቅልፍ ሳትወዱ መጠጥ ሳታበዙ፣ ገንዘብን ጠልታችሁ ተግታችሁ ሥራችሁን ፈጽሙ እኔ እናንተን ስለአመንኩ እናንተም የምታምኑትን ገንዘብ የማይወደውን፣ ድኻ የማይበድለውንና የሚረዳችሁን ሰው እያመለከታችሁኝ ከሥራው በመግባት መንግሥታችንን እርዱ ››

-
በጣም ወደኋላ የቀረን ሕዝቦች ነን ገና የሚሠራ ብዙ ሥራ ስላለ ወጣቶቻችን መማር አለባቸው

-
አባት ያለህ የአባትህን እሰጥሀለሁ፤ አባትህን መርቅ አባት የሌለህ አባትህ እኔ ነኝና ደጅ ጥናኝ

-
እኔ ቤት እንጀራ የለም እንጀራ ያለው ትምህርት ቤት ስለሆነ እሠራሁት ትምህርት ቤት ልጆቻችሁም እያስገባችሁ አስተምሩ

-
የኔ ርስት ኢትዮጵያ ናት የግል ርስት አልፈልግም ደግሞስ የተሾምነው እርስት ከተካፈልን ለሕዝቡ ማን ያካፍለዋል?

-
ሐገራችን አንድትለማ የሚቀርቡንን ሁሉ በታላቅ ደስታና በአክብሮት እንቀበላቸዋለን በሌላ ለሚመጡብን ግን ሁላችን ሳናልቅ ሀገራችንን ለባዕድ አሳልፈን እንሰጥም

-
የሚጠሉህን ሰዎች ከማጥፋት የሚጠላብህን ማጥፋት እንዲሉ የሸፈቱባቸውን የወጉአቸውንና ያሤሩባቸውን ሰዎች በጋብቻ በዝምድና ወይም ወዳጅ አድርገው ያቀርባሉ እንጂ ክፉን በክፉ መመለስና መበቀልን አይሹም
- አንድ የፈረንሳይ ዜጋ የቦታ ግዥ ፈቃድ ሲጠይቃቸው ምኒልክ በሰጡት መልስ - ‹‹ ያገሬ መሬት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ስለሆነ መሬት መሸጥ መለወጥ የሚችለው ሕዝቡ ነው ደግሞስ የውጭ ዜጎች መሬት እንዲገዙ ከፈቀድኩና ባለመሬት ከሆኑ ለኔ ምን ቀርቶ እገዛለሁ ? ›› አሉ
እቴጌ ጣይቱ ብጡል ለወራሪውና ለፋሺስቱ ጣልያን ከተናገሩት ታሪካዊ ንግግር በከፊል : -
" እኔ ሴት ነኝ ፡፡ ጦርነት አልወድም ፤ ነገር ግን ሀገሬን እንደዚህ ያለ ክብር የሚነካ ዘለፋ ከምትሸከም ጦርነትን እመርጣለሁ ፡፡ ሂድ መንገዱን ጨርቅ ያድርግልህ ! እግሩን ለጠጠር ደረቱን ለጦር አስጥቶ ደሙን ለሀገሩ ፍቅር አፍስሶ ለአፈሩ ክብር ለብሶ እሱ ወድቆ ሀገሩን የማያቆም እዚህ ያለ እንዳይመስልህ ! ሂድ! የኢትዮጲያን ሰው ባታውቀው ነው፡፡ ለሀገሩ መሞት ማለት ለሀበሻ ጌጡ ነው ፡፡ ሂድ ባሻህ ግዜ ተመለስ ተሰናድተን እንጠብቅሃለን ፡፡ ያንተን ወንድነትና የጣይቱን ሴትነትም ያን ግዜ እናየዋለን ሂድ መንገዱን ጨርቅ ያድርግልህ ፡፡ "
ስለሰውነት ክብር ፣ ስለሀገር ነፃነት ለሚቆረቆሩት ለእምዬ ምኒልክ 171 ኛ እና ለእቴጌ ጣይቱ ብጡል 175 ኛ መልካም የልደታቸው መታሰቢያ ዕለት ይሁን !!!
" ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር "

Monday, August 17, 2015

ታሪክን ስናስታውሰው !

ምስሉ ከኤድዋርዶ ገጽ የተወሰደ ነው





ይህ ቪዲ  ለዛሬው ትውልድ የሚያሳየን እውነት አለ ፡፡ ዛሬ ስለኢትዮጵያውንት ለማውራት ሰቀቀን የሆነበት ዘመን ላይ
ብንደርስም የዚህ ታዳጊ  ጥልቅ መልክት ግን ስለኢትዮጵያና ኢትዮጵያውነት መንፈስ መለስ ብላን እንድናስብ እና
ያ  የአንድንት መንፈስና ስለሀገር የማሰብ ወኔ ወዴት ጥሎን ሸሸ እንድንል ያደርጋል፡፡ በዚያውስ እምዬ ምኒልክ ዛሬ ነሀሴ 12 ቀን
ነው የተወለዱት ሲል ታሪክ ዘክሮልናል ፡፡ ታዲያ የዚህ ታዳጊ መልክት ለሳቸው ማታሰቢያ ቢሆንስ….
ማንም በአስተሳሰቡ የማይፈረጅባት ፤ በማንነቱ የማይጉላላባት፤ የሰላምና የፍቅር ሀገር ትሆን ዘንድ እመኛለሁ ኢትዮጵያ ፡፡


ደራስያንን እንደሰው ያለመመልከት አባዜ

    አለማየሁ ገላጋይ




















ፊት ለፊት ስራው፣ ከበስተጀርባ ደግሞ ህይወቱ ይገኛል፡፡ ሥራው የህይወቱ ማጣቀሻ ነው የሚሉ አሉ፡፡ በዚህም ሥራውን እንደ አነፍናፊ ውሻ አስቀድመው ህይወቱን ያንጎዳጉዳሉ፡፡ “እንዲህ ሲል የፃፈው በህይወቱ እንዲያ ስለሆነ ነው፡፡” በማለት ሥራና ህይወቱን ያጋባሉ፣ ያፋታሉ፡፡ ስለዚህ የደራሲ ቤት በሩ ቢዘጋም ከመግባትና ከመውጣት አይከላከልም፡፡ የደራሲ ደጃፍ ውሻ ቢታሰርበትም አያስፈራም፡፡ ቢታጠርም ከዘላዮች አያመልጥም፡፡ 
እኛ ዘንድ እንዲያ ለማድረግና ለመሆን የሚያስችል ሁኔታ የለም፡፡ ደራሲ የጓዳ ህይወቱ ቀርቶ አደባባይ የዋለው ሥራው እንኳን “በሙሉ አይን” አይታይም። ሀዲስ አለማየሁ፣ በዓሉ ግርማ፣ መንግሥቱ ለማ፣ ከበደ ሚካኤል፣ ፀጋዬ ገብረመድህን… የኖሩት ቀርቶ የፃፉትም የሚታየው በእሽኩርምሚት ነው። ከሥራዎቹ ፊት “ተልመጥማጮች” ያጠሩት የሙዚየም “ክር” አለ፤ አይታለፍም፡፡ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያም አለ፤ “በእጅ መንካት ክልክል ነው” የሚል፡፡ እኔ የሚገርመኝ “የተልመጥማጮቹ” በክር ማጠርና መንገር አይደለም፡፡ የእኛ አክብሮ ሥነ - ፅሁፍን በሙዚየም ህግ መጎብኘት እንጂ …፡፡ 
“የሀዲስ ዓለማየሁ ፍቅር እስከ መቃብር ተረታማ ነው” ከተባለ “ቱግ” የሚሉ “አንቀራባጮች” አሉ። “በዓሉ ግርማ ልቦለድ ያድፋፋል፤ አጨራረሱ መሰላቸት የሚታይበት የተካለበ ነው” ከተባለ የሥራው “ተሸላሚዎች” ፣ “ሐይማኖት የግል ነው፣ ለምን ይነካብናል?” በማለት ህገ መንግሥት መጥቀስ ይዳዳቸዋል፡፡ “የመንግሥቱ ለማ ግጥሞች ጥብቀትና ፍላት የሌላቸው በተሃ ናቸው” ከተባለስ? ጉዳዩን የቤተሰብ ፖለቲካ አድርገው “አብዬን?” የሚሉና የዛገ ጦር ከራስጌ የሚመዙ ሞልተዋል፡፡ “ከበደ ሚካኤል መከሩ፣ ዘከሩ እንጂ አልተቀኙም” የሚል ካለ፣ “ባባቶቻችን ደም” ይዘፈንበታል፡፡ “ፀጋዬ ገብረመድህን ግጥም እንጂ ዝሩው ያዳግተዋል” ብሎ በህይወት መኖር ያዳግታል … 
የእኛ ሥነ - ፅሁፍ መብላላት ሲገባው የሚደነብሸው ለዚህ ሳይሆን ይቀራል? ገንዘብ ያወጣሁበትን መፅሐፍ ለመግዛት፣ ጊዜ ያፈሰስኩበትን ልቦለድ (ለማንበብ)፤ ቦታ የሰጠሁትን ሥራ ለማስቀመጥ … እንዴት በሌሎች እይታ እንድገመግመው እገደዳለሁ? እንዳቅሜ ከቻልኩ “ብበላው”፣ ካልቻልኩ “ብደፋው” ከውይይት ያለፈ ከሳሽና ወቃሽ ሊመደብብኝ ይገባል?... 

“ላምባ” ፊልም መሰረቁ ከሰብዓዊ ዓላማው አስተጓጎለው ተባለ (አለማየሁ አንበሴ)

 ሌብነት እንኳ አይነት አለው !
 
 በእውነት በ”ላንባ” ፊልም ላይ የተፈጸመው ዝሪፊያ ህሊናችን ከውዴት ነው ያሰኛል፡፡
በአንድቤት ውስጥ አንድና ከዚያ በላይ በኩላሊት ህመም እየተሰቃዩ ባሉ ህማን ላይ እንደመቀለድ ነው፡፡  ….እንኳንስ ድሀው
ምንም የሌለው ገንዘብ ያለውን እያደኸየ ያለ ፤ ድንገት ማንንም የሚጥል ህመም ፤ እድሜና ጾታን የማይለይ ህመምን
ለመዋጋት የሚደረግን ጥረት የሚያኮላሽ ተግባር ….. በአውነት ያማል ፡፡ ሌብነት እንኳ አይነት አለው ፡፡
ይህን አንብባቹ ፍረዱ !!!!!!!!!!!
“ላምባ” ፊልም መሰረቁ ከሰብዓዊ ዓላማው አስተጓጎለው ተባለ

“25 ተመልካቾች ራሳቸውን ስተው ወድቀዋል”
               ፊልሙ የተመልካች አድናቆትን አትርፏል 
                                
      በመጋቢት ወር መጨረሻ ላይ ተመርቆ ለዕይታ የበቃው “ላምባ” ፊልም ተሰርቆ በኢንተርኔት በመለቀቁ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከሲኒማ ቤት የወረደ  ሲሆን ከተነሳለት ሰብዓዊ ዓላማም እንዳስተጓጎለው ተገለፀ፡፡ በእውነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ የተሰራው ፊልሙ፤ በአንድ ኩላሊት ህመምተኛ ላይ የሚያጠነጥን ሲሆን ለእይታ በቀረበባቸው ጊዜያት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተመልካች እንደነበረው ታውቋል፡፡ 
ፊልሙ በዘውዲቱ ሆስፒታል ውስጥ ለሚገነባው የኩላሊት ህክምና ማዕከል በሚሊዮን ብር የሚገመት ገቢ ለማሰባሰብ ታቅዶበት የነበረ ቢሆንም ማንነታቸው ባልታወቀ ሰዎች ተሰርቆ በኢንተርኔት በመለቀቁ ዓላማው እንደከሸፈ የፊልሙ ፕሮዱዩሰሮች ይገልፃሉ፡፡ 
ፊልሙ ከሲኒማ ቤት በምን ሁኔታ ተሰርቆ እንደወጣ ያልታወቀ ሲሆን ፕሮዱዩሰሮቹ፣ “በበርካቶች እጅ መግባቱን በማረጋገጣችን ወደ ክስ ለመሄድ እምብዛም ጥረት አላደረግንም” ብለዋል፡፡ ፊልሙ ከአብዛኞቹ ሲኒማ ቤቶች የወረደ ቢሆንም በአሁኑ ሰዓት በላፍቶ ሞልና በአምባሳደር ሲኒማ እየታየ እንደሆነ ታውቋል፡፡ 
የተመልካቹ ቁጥር በየጊዜው እየጨመረ እንደነበር የጠቆሙት የፊልሙ ደራሲና ዳይሬክተር አቶ አንተነህ ኃይሌ፤ በኩላሊት ህመምተኛ ላይ የሚያጠነጥነው ፊልም እጅግ አሳዛኝ በመሆኑ የተነሳ በተለያዩ ሲኒማ ቤቶች 25 ተመልካቾች ራሳቸውን ስተው እስከመውደቅ መድረሳቸውን ተናግረዋል፡፡ 
800ሺ ብር ገደማ እንደፈጀ የተነገረለት “ላምባ”፤ በሸገር 102.1 ሬዲዮ የ“ለዛ” ፕሮግራም “የዓመቱ ምርጥ ፊልም” ሽልማትን በሶስት ዘርፎች በመመረጥ እየመራ እንደሚገኝ አዘጋጁ ጋዜጠኛ ብርሃኑ ድጋፌ ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡ 
“ፊልሙን የሰራነው ለምናከናውነው የበጎ አድራጎት ስራ ማነቃቂያ እንዲሆን ነበር” ያለው የፊልሙ ፀሐፊና ፕሮዱዩሰር አንተነህ ኃይሌ፤ በ4 ወራት የሲኒማ ቤት ቆይታው ለኩላሊት ህክምና ማዕከል ማሰሪያ ድጋፍ (በአጭር የስልክ መልዕክት) ወደ 300ሺ ብር የሚጠጋ ገቢ ማሰባሰብ እንደተቻለ ጠቁሟል፡፡ 
በአሁን ሰዓት በዘውዲቱ ሆስፒታል  የኩላሊት ህክምና ማዕከል ህንፃ ግንባታ ተጠናቆ የህክምና መሳሪያዎችን ለመግዛት የሚያስችለውን ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለማግኘት ፊልሙን ማሳየት ጨምሮ የተለያዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሞች ታቅደው  እንደነበር አቶ አንተነህ ለአዲስ አድማስ አስረድቷል፡፡ 
ፊልሙ ባይሰረቅ ኖሮ ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ በተለያዩ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች በማሳየት እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር ገቢ ለማሰባሰብ ታስቦ እንደነበር ፕሮዱዩሰሮቹ ገልፀዋል፡፡ በተለይ በመጪው መስከረምና ጥቅምት ወራት የመንግስት ባለስልጣናትን ጨምሮ ለተለያዩ ባለሀብቶችና በውጭ አገር ለሚገኙ ኢትዮጵያውያንም በማሳየት ላቅ ያለ ገቢ ለማስገኘት ታስቦ ነበር፡፡
ከፊልሙ ይገኛል የተባለው ገቢ ከዚህ በኋላ የሚሳካ ባይሆንም የኩላሊት ማዕከሉን ግንባታ ለማስፈፀምና ቁሳቁሶችን ለማሟላት ህብረተሰቡ በስፋት የሚሳተፍበት የቴክስት መላኪያ ቁጥር ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ ይፋ እንደሚደረግ ታውቋል። 
ከጀርመን ሃገር በተገኘ ብድር የተገዙ 20 ያህል የኩላሊት ህክምና ማሽኖች በቅርቡ ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው ይተከላሉ ያሉት አቶ አንተነህ፤ ሌሎች ማሽኖችን ለማስገባት ለሚያስፈልገው 60 ሚሊዮን ብር ደግሞ የተለያዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሞች እንደታቀዱ ገልፀዋል፡፡
በተመልካቾች ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈው “ላምባ” ፊልም መሰረቁ በአገሪቱ የፊልም ኢንዱስትሪ ዕድገት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚያሳድር የፊልም ባለሙያዎች ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ በ“ላምባ” ፊልም ላይ በመሪ ተዋናይነት የሚሰራውን ዕውቁን አርቲስት ግሩም ኤርሚያስ ጨምሮ ሌሎች በርካታ አርቲስቶች ተውነውበታል፡፡
http://www.addisadmassnews.com/