Monday, June 22, 2015

ዳሪዮስ ሞዲ እና ትዝታዎቹ


ጥንቅር፡ አፈንዲ ሙተቂ
-----

ዳሪዮስ ሞዲ በዛሬው ዕለት ይህቺን ዓለም በሞት ተሰናብቷል፡፡ ያ ጣፋጭ ድምጹ ዳግመኛ ላይሰማ በዚያው ጠፍቷል፡፡ ሆኖም በህይወት በነበረበት ዘመን በትዝታዎቹና በግል ህይወቱ ዙሪያ ከተለያዩ መጽሔቶች ጋር ቃለ-ምልልስ አድርጓል፡፡ እኔም ትዝታዎቹን እንደሚከተለው አጠናቅሬአለሁ፡፡

=== ትውውቅ==
በቅድሚያ እድሜአቸው ከሃያ ዓመት በታች ለሆነ ወዳጆቻችን አጭር ማስተዋወቂያ እነሆ ብለናል፡፡
“ዳሪዮስ ሞዲ” በኢትዮጵያ ታሪክ ከታዩ ባለግርማ ሞገስ የሬድዮ ጋዜጠኞች አንዱ ነው፡፡ ይህ ጋዜጠኛ በተለይ የሚታወሰው
ሀ/. ግንቦት 13/1983 ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለ-ማሪያም ሀገር ጥለው መሄዳቸውን በገለጸበት ዜና
ለ/. ግንቦት 20/1983 ኢህአዴግ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ ድምጹን ያሰማ የመጀመሪያው ጋዜጠኛ በመሆኑ እና በሌሎችም የሬድዮ ጣቢያው ታሪካዊ ኩነቶች ነው፡፡ በተጨማሪም በዘመነ ደርግ እና በኢህአዴግ ዘመን የመጀመሪያው ዓመት ከመንግሥት የሚተላለፉ መግለጫዎችንና አዋጆችን የሚያሰማው በአብዛኛው እርሱ ነበር፡፡
===== ዳሪዮስና የ“ቡሽቲ” ወሬ===
ዳሪዮስ አራት ኪሎ አንድ ካፍቴሪያ ውስጥ የገጠመውን እንዲህ ያጫውተናል፡፡
“ቡና ቤቱ ውስጥ ቡና እየጠጣሁ ነው፡፡ ሁለት ሰዎች ከኔ ፈንጠር ብለው ተቀምጠዋል፡፡ ከአንደኛው ጋር በዓይን እንተዋወቃለን፡፡ አንደኛውን ግን አላውቀውም፡፡ ከኔ ጋር የማይተዋወቀው ሰዉዬ “የሬድዮውን ድምጽ ከፍ አድርጉት” አለ፡፡ ተደረገለት፡፡ በአጣጋሚ እኔ የሰራሁት ፕሮግራም እየተላለፈ ነበር፡፡ እርሱም በአውስትራሊያ የተካሄደውን ውስጥ የጽንስ ማሳደግ ፕሮግራም የሚመለከት ነበር፡፡ ይኸውም አንድን ወንድ ሆዱን ቀደው ጽንስ ይከቱበታል፡፡ ከዚያም ሆዱን ይሰፉታል፡፡ ጽንሱ እያደገ ሄደ፡፡ የሰውየውም ባህሪይ ጽንሱ ባደገ ቁጥር የሴት ባህሪይ እየመሰለ ይሄዳል፡፡ ይህንን ነበር ያቀረብኩት፡፡
ሰውየው ይህንን ሲሰማ በመደነቅ “ከየት እንደሚያመጣው አይታወቅም፡፡ ትሰማዋለህ? ይሄ ቡሽቲ መሆን አለበት” አለ፡፡ ከርሱ ጋር የነበረው ሰውዬ (ከኔ ጋር በዐይን የሚተዋወቀው) ወሬውን እንዲያቆም ቢጠቅሰው አልሆነለትም፡፡ ጭራሽ ሰውዬው ወደኔ ዞሮ “አይመስልህም ወንድም?” አለኝ፡፡ እኔም “አዎ ልክ ነህ” አልኩት፡፡ “እንዴት ወንድ ልጅ ያረግዛል ብሎ ያወራል፡፡ አወቅሽ አወቅሽ ቢሏት መጽሐፍ አጠበች እንደሚባለው ነው፡፡ ሁለተኛ ይህንን ሰው አልሰማውም” አለና እንደገና ወደኔ ዞሮ “ይሄ ቡሽቲ አይደለም?” አለኝ፡፡ “ነው” አልኩት፡፡ በወቅቱ ከመቀበል በስተቀር ምንም መልስ የለኝ፡፡
(አቢሲኒያ መጽሔት፡ ቅጽ 1፤ ቁጥር 2፤ የካቲት 1985)
=====ዳሪዮስ እና ግንቦት 13===
ግንቦት 13/1983፡፡ ከቀኑ 6፡00 ሰዓት፡፡ የኢትዮጵያ ድምጽ ብሔራዊ አገልግሎት (የአሁኑ የኢትዮጵያ ሬድዮ) ማንም ያልጠበቀው ዜና አስተላለፈ፤ እንዲህ የሚል፡፡
“ለረጅም ዓመታት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ሲካሄድ የነበረው የርስ በርስ ጦርነት ያስከተለውን የኢትዮጵያዊያን ህይወት መጥፋትና ከኑሮ መፈናቀል ለማስቀረት በልዩ ልዩ መልክ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል፡፡ ሆኖም ችግሩ አልተቃለለም፡፡ ይልቁንም ወደ ባሰ ደረጃ እየተሸጋገረ በመሄድ ላይ ይገኛል፡፡ ስለዚህ ደም መፋሰስ እንዲቆምና ሰላምም እንዲሰፍን በልዩ ልዩ ወገኖች የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ከስልጣን መውረዳቸው እንደሚበጅ የታመነበት ስለሆነ ይህንኑ በማመዛዘን ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለማሪያም ከስልጣናቸው ወርደው ከኢትዮጵያ ውጪ ሄደዋል”
ዜናውን ያነበበው ድምጸ መረዋው ዳሪዮስ ሞዲ ነበር፡፡ ዳሪዮስ ከኢትኦጵ መጽሔት ጋር ባደረገው ቃለ-ምልልስ በጊዜው የነበረውን ሁኔታ እንደሚከተለው ገልጾታል፡፡
ኢትኦጵ፡- ዳሪዮስ ያንን ዜና ስታነበው ፍርሃት አልተሰማህም?
ዳሪዮስ፡ ለምን ትንሽ ሰፋ አድርጌ አልገልጽልህም? በወቅቱ የማስታወቂያ ሚኒስትር የነበሩት አቶ አብዱልሓፊዝ ዩሱፍ ጋዜጠኛ ጌታቸው ኃይለማሪያምን ወደ ቢሮአቸው ያስጠሩታል (ጌታቸው ያኔ የቅርብ አለቃዬ ነበረ)፡፡ ጌታቸው ከሚኒስትሩ ቢሮ ተመልሶ እንደመጣ “ቆይ ከዚህ እንዳትሄድ” አለኝ፡፡ “ለምን” ስለው “የሚነበብ ዜና አለ” አለኝ፡፡ “እኔ እኮ ተረኛ አይደለሁም” አልኩት፡፡ “አይ! አንተ ነህ የምታነበው አለኝ”፡፡ እና በዚያው አነበብከኩት፡፡
ኢትኦጵ፡ ዜናው ምን እንደሆነ አስቀድሞ አልተነገረህም?
ዳሪዮስ፡ በፍጹም! እንኳንስ እኔ ጌታቸው ራሱ ያወቀ አልመሰለኝም፡፡ ብቻ በቃ “የሚነበብ ዜና አለ” ነው የተባልኩት፡፡ ስድስት ሰዓት ሲደርስ ስቱዲዮ ገባሁ፡፡ ያኔ ወረቀቱን ሰጡኝ፡፡ “ለሀገርና ለህዝብ ደህንነት ሲባል ከሀገር እንዲወጣ ተደርጓል” ይላል፡፡
ኢትኦጵ፡-አልደነገጥክም?
ዳሪዮስ፡ በጭራሽ! እንዲያውም እውነት ለመናገር ትልቅ ደስታ ነው የተሰማኝ፡፡ ልክ አንብቤ እንደጨረስኩ “አሁን ወደምትፈልግበት መሄድ ትችላለህ ተባልኩ”፡፡
(ኢትኦጵ መጽሔት፡ ቅጽ 3- ቁጥር 36፤ ግንቦት 1994)
====የዳሪዮስ ልጆች====

Tuesday, April 14, 2015

የትንሳኤ ስጦታ! የብላቴናው አስደማሚ ሰብዓዊ ተግባር

 Written by  አለማየሁ አንበሴ



   በየሁለት ሣምንቱ እሁድ መርካቶ አንዋር መስጊድ አካባቢ 4 ሰአት ግድም የደረሰ ማንም ሰው አንድ የተለየ ክስተት መመልከቱ አይቀርም፡፡ ነገሩ አዲስ የሚሆንበት ለእንደኔ ዓይነቱ እንግዳ እንጂ የአካባቢው ነዋሪዎችማ ለምደውታል፡፡ ላለፉት ሦስት ዓመታት ሲካሄድ የቆየ አስደማሚም አስገራሚም ሰብዓዊ ተግባር ነው፡፡ ከልጅነቱ ጀምሮ በአካባቢው የሚታወቀው ብላቴናው አስመሮም ተፈራ፤ በመርካቶ ዙሪያ በየጎዳናው የወደቁ የአዕምሮ ህሙማንን እያነሳ ገላቸውን ያጥባቸዋል፡፡ ፀጉራቸውን ይላጫቸዋል፡፡ አዲስ ልብስ ያለብሳቸዋል፡፡ ምግብም ያበላቸዋል፡፡ 
የአዕምሮ ህሙማኑን የሚያጥብበት ሰወር ያለ ስፍራ ባለመኖሩ አውራጐዳና ላይ እርቃናቸውን ሲያጥባቸው ማየት የተለመደ ትዕይንት ነው፡፡
አስመሮምን ከልጅነቱ ጀምሮ እንደሚያውቁት  የሚናገሩት የ70 ዓመቱ የአካባቢው አዛውንት አቶ መሃመድ ጀማል፤ “ሰፈር ውስጥ ሲላላክልንና ሲያገለግለን ያደገ ልጅ ነው፤ አሁንም ሰዎች የሚፀየፏቸውን የአዕምሮ ህሙማን ለመንከባከብ የሚያደርገው ጥረት የታዛዥነቱና የቀናነቱ ነጸብራቅ ነው” ይላሉ፡፡ በልጅነቱ ከቤተሰቦቹ ተለይቶ በችግር ማደጉን እናውቃለን ያሉት አዛውንቱ፤ ያለፈበትን ህይወት አስታውሶ እነዚህን ምስኪኖች በሽታ አለባቸው፣ ተባያቸው ይተላለፍብኛል ሳይል ላለፉት ሦስት ዓመታት በቋሚነት ሲያጥባቸው፣ ሲያለብሳቸውና ሲመግባቸው ተመልክቻለሁ” ሲሉ እማኝነታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ብላቴናው አስመሮም (ባሪያው) የተወለደው ከረዩ ሰፈር ቢሆንም ከቤተሰቦቹ ጋር በተፈጠረው አለመግባባት ገና የ8 ዓመት ህፃን ሳለ ነበር ወደ ጎዳና የወጣው፡፡ የአሜሪካን ግቢ ነዋሪዎች ባደረጉለት ድጋፍም በልጅነቱ በተለያዩ ስራዎች ላይ ለመሰማራት እንደቻለ ይናገራል። አስመሮም በየሁለት ሳምንቱ እሁድ ገላቸውን የሚያጥባቸው፣ ፀጉራቸውን የሚላጫቸውና ልብሳቸውን የሚቀይርላቸው እንዲሁም ምግብ የሚያበላቸው የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር 25 ደርሰዋል፡፡ በዚህም የተነሳ እየተሳቀቅሁ በአደባባይ ርቃናቸውን ሳጥባቸው ተገድጄአለሁ ይላል፡፡ ይሄን ሰብዓዊ ተግባር ለመፈፀም ወጪው ከፍተኛ እንደሚሆን መገመት አያዳግትም፡፡ እሱ ደግሞ መኪና አጥቦ አዳሪ ነው፡፡
አስመሮም እንደሚለው፤ የታክሲ ሹፌሮች ባይኖሩ ኖሮ ይሄን በጐ ተግባር ለማከናወን አይችልም ነበር፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ ባለፈው እሁድ በስፍራው ተገኝቶ ለህሙማኑ የሚደረገውን እንክብካቤ ከተመለከተ በኋላ ከወጣት አስመሮም ተፈራ ጋር በሰብዓዊ ተግባሩ ዙሪያ ተከታዩን አስገራሚና አስደማሚ ቃለምልልስ አድርጓል፡፡ 

Monday, April 6, 2015

ኢትዮጵያዊው ዶ/ር ኤሌክትሮን “የዓለማችን ልዩ ስም” ውድድርን እየመሩ ነው

ከኦባማ ቀጥሎ በአሜሪካ ከፍተኛው ደመወዝ ተከፋይ ነበሩ
ከ2ሺ በላይ የተሳኩ ቀዶ ህክምናዎችን አከናውነዋል 
ወንድሞቻቸው፡- ፕሮቶን፣ ኒውትሮን፣ ዲዩትሮን፣ ኤሌክትሮን እና ፖሲትሮን ይባላሉ

















ትውልደ ኢትዮጵያዊው ዶክተር ኤሌክትሮን ክበበው፤ ለ33ኛ ጊዜ በመካሄድ ላይ በሚገኘው የ2015 “የዓመቱ የዓለማችን ልዩ ስም” ውድድር ላይ ከፍተኛ ድምጽ በማግኘት በቀዳሚነት እየመሩ እንደሆነ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል፡፡
በአለማቀፍ ደረጃ በሚካሄደው በዚህ ውድድር ላይ ዘንድሮም የተለያዩ አገራት ዜጎችና በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ላይ የተሰማሩ 64 ግለሰቦች ያልተለመዱ ስሞች ለውድድር የቀረቡ ሲሆን ኢትዮጵያዊው ዶ/ር ኤልክትሮን ክበበው፤ በ1ሺህ 132 ድምጽ፣ በ89.6 በመቶ ውጤት በቀዳሚነት በመምራት ላይ ይገኛሉ፡፡
በኢሜልና በተለያዩ መንገዶች ከቀረቡለት በርካታ ለየት ያሉ ስሞች 64 ያህሉን በመምረጥ፣ ለአንድ ሳምንት ያህል በድረ ገጽ አማካይነት ድምጽ እንዲሰጥባቸው የሚያደርገው የውድድር ኮሚቴው፤ የመጨረሻውን ውጤት ከጥቂት ቀናት በኋላ ይፋ እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡
የሰማይ እንሽላሊት፣  ጣፋጭ ቡና፣ ዳላስ፣ ቶክዮ፣ ቴኒስ እና የመሳሰሉ የአገር፣ የቦታ፣ የእቃ፣ የሰብል ወዘተ መጠሪያዎችን የያዙ የተለያዩ አገራት ዜጎች በዘንድሮው ውድድር እንደተሳተፉ አወዳዳሪዎቹ ገልጸዋል፡፡
በዘንድሮው ውድድር ከፍተኛ ድምጽ በማግኘት በመምራት ላይ ለሚገኙት የ47 አመቱ ዶ/ር ኤሌክትሮን ይህን ስም ያወጡላቸው፣ ኤሌክትሪካል ኢንጂነር የሆኑት ኢትዮጵያዊው አባታቸው አቶ ክበበው ነበሩ፡፡
ልጆቻቸው የእሳቸውን ፈለግ ተከትለው በሳይንሱ ዘርፍ ላይሰማሩ ይችላሉ የሚል ስጋት ያደረባቸው አቶ ክበበው፤ በልጆቻቸው ልቦና ውስጥ ገና በለጋ እድሜያቸው የሳይንስን ስሜት ለማስረጽ በማሰብ ነው፣ ባልተለመደ ሁኔታ ለልጆቻቸው ከኤሌክትሪሲቲ ጋር የተያያዙ ስሞችን ያወጡት፡፡
አቶ ክበበው፤ ለአምስቱ ልጆቻቸው ፕሮቶን፣ ኒውትሮን፣ ዲዩትሮን፣ ኤሌክትሮን እና ፖሲትሮን የሚሉ ስሞችን አውጥተዋል፡፡ ዶ/ር ኤሌክትሮን በስማቸው ብቻ አይደለም የሚለዩት፡፡ ከስማቸው በላይ ብዙዎችን ያስገረመው፣ በህክምና ሙያቸው የአሜሪካ መንግስት የሚከፍላቸው ዳጎስ ያለ ደመወዝ ነው ይላል ድረ-ገጹ፡፡
ከአራት አመታት በፊት “ዊኪኦርግቻርትስ” የተባለ ተቋም “የአመቱ የአሜሪካ መንግስት 1000 ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋዮች” በሚል ባወጣው ዝርዝር ውስጥ፣ ዶ/ር ኤሌክትሮንን ከአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ቀጥሎ ከፍተኛ ደመወዝ የሚያገኙ የመንግስት ሰራተኛ በማለት በሁለተኛነት አስቀምጧቸዋል፡፡
በአዲስ አበባ በሚገኘው ቅዱስ ዮሴፍ ትምህርት ቤት የተማሩት ዶ/ር ኤሌክትሮን ክበበው፤ በአሜሪካ ሳንፍራንሲስኮ ከሚገኘው ዪኒቨርሲቲ ኦፍ ካሊፎርኒያ በህክምና የተመረቁ ሲሆን የአሜሪካን ቦርድ ኦፍ ሰርጀሪን የቀዶ ህክምና ሰርተፊኬትም አግኝተዋል፡፡ 
ላለፉት 20 አመታት በሳንፍራንሲስኮ በኢንዶክሪንና ታይሮይድ ካንሰር ዘርፍ የአጠቃላይ ቀዶ ህክምና አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙት ዶክተሩ፤ በአሜሪካ ብሄራዊ የካንሰር ኢንስቲትዩት፣ የካንሰር ምርምር ማዕከል የኢንዶክራይን ኦንኮሎጂ ቅርንጫፍ ሃላፊ ሲሆኑ የካንሰር ጄኔቲክስ ክፍሉንም በበላይነት በመምራት ላይ ይገኛሉ፡፡
ዶክተሩ በእስካሁኑ የሙያ ዘመናቸው ከሁለት ሺህ በላይ የተሳኩ ቀዶ ህክምናዎችን ያከናወኑ ሲሆን ከ150 በላይ የጥናት ጽሁፎችንና መጽሃፍትን ለህትመት እንዳበቁ “ብሬኪንግጎቭ” የተሰኘ ድረገፅ አመልክቷል፡፡
http://www.addisadmassnews.com/

Thursday, April 2, 2015

Letter from Ethiopia: back and forth

Philip Rayner
Despite breakneck economic regeneration, Addis Ababa retains many of its familiar charms and frustrations






















A busy market contains all the sights, sounds and smells of Addis Ababa. Photograph: Robert Harding World Imagery/Alamy

I am not sure why I like Ethiopia so much. In part, I think it is the sights, sounds and smells that are so evocative. Watching a blood-red sun beginning to set through the haze that hovers over Addis Ababa, watching the black kites swoop between the buildings, listening to the sounds of traffic, Ethiopian pop music and the odd chicken or two, plus the smells of wood smoke, roasting coffee, cheap diesel and something else, indescribable, but essentially African, I remember why I like this country so much.

I am also attracted by the people. In most Ethiopians there is a joy and optimism. They believe that they are on the cusp of great things: becoming a middle-income country, surfing the “knowledge superhighway”. Every state company and organisation now has a vision and mission that they publicise. I noticed that at Mekelle airport their vision was to become “the best airport in Africa”; several Ethiopian universities share the vision to become “the best university in Africa”. There is no sense of irony or scepticism: this is what they want to do and they will try their best to achieve it – anything is possible, “God willing”.

I am returning after an absence of several years and catching up with old friends like Solomon, who works in a private university. In many ways it all seems very familiar: the same donkeys and goats roaming the streets, the shoeshine boys, and people as friendly and chatty as ever.

However, the area of Addis where I am staying has changed a lot. There is a two-track railway being built down the middle of the main road; the central reservation that used to divide the two lanes of traffic that had some trees, some shrubs and a few men sleeping is gone. Many of the small family businesses, shops and restaurants have either been knocked down or closed down due to lack of business. All along the main road enormous buildings are being constructed and Solomon tells me that he is worried about the infrastructure needed to support them. Whether they become offices, colleges, hospital or shopping malls they will need additional electricity, internet connectivity, water supply and sewage but there is no evidence that these already over stretched services are going to be upgraded.

Meskel Square in the centre of Addis seems to have lost a lot of its glamour (if that’s the right word); the railway carves through the air, at eye-level with the stand where the leaders of the Derg used to stand to watch their military displays. The artificial palm trees with the flashing lights and the giant TV screen have gone. Now it seems to be a giant coach park.


I am off for a stroll through the evening warmth, the dust and the rubble. I will probably stop for a drink. A fresh squeezed mango juice? A freshly brewed macchiato? Can’t decide!


Tuesday, March 31, 2015

ፋኖስና ብርጭቆ


አንድ የፋኖስ መብራት በግብሩ የኮራ፤
እንዲህ ሲል ተጣላ ከብርጭቆ ጋራ፡፡
‹‹እኔ ነኝ መብራቱ ብርሃን የምሰጥ፤
ጨለማን አጥፍቼ የምገላልጥ፡፡
አንተ ግን ከፊቴ እንዲህ ተደንቅረህ፤
ዙሪያዬን ከበኸኝ እንዲያው ተገትረህ፡፡
አልገባኝም ከቶ የምትሰራው ስራ፤
ብርሃኔ ሩቅ ደርሶ ደምቆ እንዳያበራ፤
አንተን ፈጠረብኝ መንገድ የምትዘጋ፡፡
እንቅፋት እየሆንክ ስራዬን አታጥፋ
ገለል በል ከፊቴ ብርሃኔ ይስፋፋ፡፡››
‹‹አገልግሎቴማ ከሆነብኝ ጥፋት፤
እውነት ላንተ ከሆንኩህ እንቅፋት፡፡
ልሂድልህ›› ብሎ ሲለቅለት ቦታ፤
ከጎን የነፈሰ የንፋስ ሽውታ፣
መጣና መብራቱን አጠፋው ባንዳፍታ፡፡
አጭር እየሆነ ተመልካችነቱ፣
መለየት አቅቶት ጥቅሙን ከጉዳቱ፣
እወቁኝ እወቁኝ እያለ ሲነሳ
ሰውም እንደዚሁ ያመጣል አበሳ፡፡

(/ ከበደ ሚካኤል)

Monday, March 30, 2015

"ከዝንጀሮም እንገኝ ከአዳምና ሄዋን ወንድምና እህት ነን» የክብር ዶ/ር ዙምራ ኑሩ"

በቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
አንጋፋው የአውራምባ ማህበረሰብ መስራች የክብር ዶክተር ዙምራ ኑሩ እሱ «ምንም እንዳልሰራሁ ሁኖ ይሰማኛል» ቢልም ሀሳቡ መሬት ወርዶ ፣ ዘር አፍርቶ ከዜሮ ቀና ወደ ማለት ሲጓዝ አይቷል ። እርሱ በቁሙ እያለ ማህበረሰቡ በንቀትና በጥላቻ ከመታየት ወጥቶ እንደ አንድ የባህል ቅርስ ሊጎበኝ በቅቷል ። በራሱ የህይወት ፍልስፍና ማህበረሰቡን ያነፀው ይህ ሰው ለእኛ ባይደንቀንም ነጮቹ ግን ህይወትና ፍልስፍናው አስደምሟቸው የክብር ጥሪ ያደርጉለታል ። ከወራት በፊት ከጥሪዎቹ አንዱን ተቀብሎ ፈረንሳይ ውስጥ የክብር ጉብኝት አድርጎ በ10 ቀናት ቆይታው በሔደበት የተናገረው ከቁም ነገር ተቆጥሮለት በፈረንሳይኛና በእንግሊዘኛ ቋንቋዎች ዶክመንታሪ ተሰርቶለት ተመልሷል ። በተመሳሳይም ከተለያዩ ሀገራት የጉብኝት ጥያቄ ይቀርብላታል ።
ዙምራ ሰሞኑን አዲስ አበባ በመጣ ጊዜ አግኝቶኝ የመጣበትን ጉዳይ ከተወያየን በኋላ ለኢትዮ ዴይሊ ፖስት ዌብ ሳይት አንባብያን የሚከተለውን አውግተናል ፡፡
zumera






















 ኢትዮ ዴይሊ ፖስት ፡- ዙምራ አዲስ አበባ እንዴት መጣህ ?
 ዙምራ፡- በመኪና ተሳፍሬ ነዋ ።
 ኢትዮ ዴይሊ ፖስት፡ በመኪናማ ነው ። ለምን አላማ መጣህ ማለቴ ነው እንጂ ።
 ዙምራ፡- አላማዬ ብዙ ነው ። እናንተ ጋዜጠኞችንም ልወቅሳችሁ ነው የመጣሁ ።
 ኢትዮ ዴይሊ ፖስት፦ ምን አደረግን ?
  ዙምራ፡- ጥሩነትና መጥፎነትን አበጥራችሁ ሕዝቡ ልብ ውስጥ አላደረሳችሁም ። ሰው በጥሩው ብቻ አይማርም ።    ከክፋትም ይማራል ። የእናንተ ድርሻ ፣ የምሁራኑም ድርሻ ክፉ ከደግ እንዲለይና እንዲታይ ማድረግ ነው ፡፡     እናንተ ናችሁ ሀገርን የምትለውጡት ። እናንተ ናችሁ ሀሳብን በጥሩ መሬት ላይ እንዲዘራ የምታደርጉ ። ይህን ነው የምጠይቃችሁ ። እናንተ መልካም ዘር ናችሁ ብላችሁ አምናችሁ መች ወደሰው አደረሳችሁን መች ሀሳባችን ሰውጋ ደረሰ 

Tuesday, March 24, 2015

የህፃናት አምባ ልጆች ትዝታና ቁጭት

Written by  መታሰቢያ ካሳዬ
  ወቅቱ 1973 ዓ.ም ነበር፡፡ አገሪቱ ከተለያዩ የውስጥና የውጪ ኃይሎች ጋር ጦርነት ውስጥ የገባችበት ጊዜ ነው፡፡ በርካታ ኢትዮጵያውያን ወታደሮች ልጆቻቸውን ያለ አሳዳጊ ጥለው በየጦር ሜዳው ወድቀዋል፡፡ አሳዳጊና ተንከባካቢ ያጡት ህፃናት በየጎዳናው መውደቃቸው ያሳሰበው የደርግ መንግስት፤ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት በነበሩት መንግስቱ ኃይለማርያም ልዩ ትዕዛዝ የአብዮታዊት ኢትዮጵያ ህፃናት አምባ ተቋቁሞ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ 
በቀድሞ አጠራር በሸዋ ክፍለ ሃገር ሀይቆችና ቡታጅራ አውራጃ፣ በአላባ ቁሊቶ ወረዳ፣ አላጌ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ወላጆቻቸውን በጦርነትና በሌሎችም ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ አደጋዎች ያጡ ህፃናትን ተቀብሎ መሰረታዊ ፍላጎቶቻቸውን በማሟላት፣ በትምህርትና በሥነ ምግባር ኮትኩቶ የማሳደግን ዓላማ አንግቦ የተቋቋመው አምባው፤ “ሰብለ አብዮት”፣ “መስከረም ሁለት ኦጋዴን”፣ “ዘርዓይ ደረስ” እና “መንግስቱ ኃ/ማርያም” በተባሉ 5 መንደሮች የተከፋፈለ ነበር፡፡ 
አምባው ገና ከተወለዱ ህፃናት ጀምሮ በተለያዩ የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ህፃናትን ተቀብሎ እያሳደገ ያስተምርና ዕድሜያቸው 18 ዓመት ሲሞላ (የ12ኛ ክፍል ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁ) ከማሳደጊያው ይሰናበታሉ፡፡ ህፃናቱ አምባውን ለቀው በሚወጡ ጊዜ በስነ ምግባር የታነፁ እንዲሆኑና በማህበራዊ ህይወታቸውም የመገለል ስሜት እንዳያድርባቸው ልዩ የምክር አገልግሎት ይሰጣቸው እንደነበር የቀድሞው የአምባው ልጆች ያስታውሳሉ፡፡ በትምህርታቸው ጥሩ ውጤት ያገኙ ተማሪዎች አንድም ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ይገባሉ አሊያም ወደ ውጪ አገር (በአብዛኛው ኩባና ራሺያ) እየሄዱ ይማሩ ነበር፡፡ በ1983 ዓ.ም የአምባው መስራችና ህፃናቱ ሁሉ ”አባታችን“ እያሉ የሚጠሯቸው የአገሪቱ መሪ ፕሬዚዳንት መንግስቱ ኃ/ማርያም አገር ጥለው መውጣት ለአምባው ህፃናትና ሰራተኞች ትልቅ ዱብ እዳ ነበር፡፡ 
የአምባው ህፃናት መሳጭና መልእክት አዘል በሆኑት ህብረ ዝማሬዎቻቸው በእጅጉ ይታወቁ ነበር፡፡ በታዋቂዋ ገጣሚ አለምፀሐይ ወዳጆ ክትትልና የጥበብ ስልጠና ይደረግላቸው የነበሩት የአምባው ልጆች፤ “የጀግና ፍሬ” በተሰኘ የኪነት ቡድን ታቅፈው በየጊዜው ለታዳሚዎች የተለያዩ ኪነ ጥበባዊ ዝግጅቶችን ያቀርቡ ነበር፡፡ በዚህ ቡድን ተዘጋጅተው ለአድማጭ ጆሮ ከበቁትና ተወዳጅነትን ካገኙት ስራዎቻቸው መካከል “ፀሐዬ”፣ “የጀግና ልጅ ጀግና” እና “እርግቢቱ ሂጂ” የሚሉት ይጠቀሳሉ፡፡ 
በ1970ዎቹ መገባደጂያና በሰማንያዎቹ መጀመሪያ ላይ አብዛኛው ታዳጊ እኒህን መዝሙሮች ከህዝብ መዝሙር ባልተናነሰ ያውቃቸው ነበር፡፡ በቀድሞዎቹ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ጣቢያዎችም መዝሙሮቹን በተደጋጋሚ መስማት አዲስ ነገር አልነበረም፡፡ የደርግን ውድቀት ተከትሎ ግን መዝሙሮቹ ታሪክ ሆነው ተረሱ፡፡ ከብዙ ዓመታት በኋላም በቅርቡ እኒህ ሥራዎች በከፊል የተካተቱበት ሲዲ ታትሞ መውጣቱ ተሰምቷል፡፡ 
እኔም አጋጣሚውን በመጠቀም የሙዚቃ ሥራው አስተባባሪ የሆኑትንና የአምባው ልጆች የነበሩትን መቅደስ ተመስገን እና ጆኒ መርጊያ ስለ ህፃናት አምባው፣ ስለ አስተዳደጋቸው፣ በተለይ ከፕሬዚዳንት መንግስቱ ጋር ስለነበራቸው ቁርኝትና ከአገር መውጣታቸውን ሲሰሙ ስለተፈጠረባቸው ስሜት እንዲሁም ስለ መዝሙሮቻቸው እንዲያወጉኝ ጠየቅኋቸው፡፡ በደስታ ፈቃደኝነታቸውን ገለፁልኝ።