Tuesday, September 12, 2017

ማር እስከ ጧፍ (ፍቅር እስከ መቃብር)


የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት የሚጀምረው ስንት ሰዓት ላይ ነው?



በዲያቆን ዳንኤል ክብረት




ዓርብ ለቅዳሜ ምሽት፣ጳጉሜን አምስት 2002 / ማታ በኢትየጵያ ቴሌቭዥን ይተላለፍ የነበረውን የአዲስ ዓመት ዋዜማ እያየሁነበር፡፡ ከአሜሪካ የገባሁት በዚያው ቀን ነበርና ዕንቅልፌ ሊስተካከልልኝ ስላልቻ በደንብ ነበር የተከታተልኩት፡፡ እኩለ ሌሊት ሊደርስ ሲል ግን አንድ አሳዛኝ ነገር ተከሰተ፡፡ የማከብራቸው አርቲስቶች ወደ መድረኩ ተሰባስበው ወጡና በዚያች ታሪካዊት ቀን ታሪካዊውን ስሕተት ሰሩት፡፡ እኩለ ሌሊት ስድስት ሰዓት ሊሆን ሽርፍራፊ ሰኮንዶች ሲቀሩ «አዲሱ ዓመት ሊገባ ስለሆነ እንቁጠር» አሉና ወደ ኋላ አሥር፣ ዘጠኝ፣ ስምንት፣እያሉ እስከ ዜሮ ቆጠሩ፡፡ 
.
ከዚያም ከምሽቱ ስድስት ሰዓት ላይ አዲሱ ዓመት ገባ ብለው አወጁ፡፡ «የሊቃውንቱ ስሕተት እድሜ ሲያገኝ ሕግ ይሆናል» ይላሉ፡፡ በጥንት ጊዜ አውስትራልያ የገባ አንድ አውሮፓዊ አይቷት የማያውቅ አዲስ ፍጡር ያይና የሀገሬውን ነዋሪ «ይህቺ እንስሳ ማን ትባላለችብሎ ይጠይቀዋል፡፡ ያም የሀገሩ ነዋሪ «ካንጋሮ» ብሎ መለሰለት፡፡ ያም ሰው «ካንጋሮ» የምትባል እንስሳ አገኘሁ ብሎ ለዓለም ተናገረ፡፡ በሀገሬው ቋንቋ ግን «ካንጋሮ» ማለት «አላውቅም» ማለት ነበር፡፡ አንድ ሞኝ የተከለውን አምሳ ሊቃውንት አይነቅሉትም እንዲሉ ይሄው ስሟ ሆኖ ቀረ፡፡

“መሰንቆ እና ብትር” ከበዕውቀቱ ሥዩም

መሰንቆ እና ብትር (ወግ)

መሰንቆ እና ብትር
ከበዕውቀቱ ሥዩም
.
አያችሁት ብያ፣ የኛን እብድ፤
አምስት ጋሞች ይዞ፣ ጉራምባ ሲወርድ …”
አዝማሪ ጣፋጭ [1845 .]
.
የዳሞቱ መስፍን ደጃዝማች ጎሹ እና የቋራው ፋኖ ደጃዝማች ካሳ በኅዳር 19 1845 . ጉራምባ ላይ ጦርነት ገጠሙ። ካሳ፣ ከጥቂት ታማኝ ጭፍሮቻቸው ፊት ተሰልፈዋል። ጎሹም፣ በተለመደው የጀብድ መንገድ ከሰራዊታቸው ፊት ለፊት ቀድመው፣ ሲዋጉና ሲያዋጉ ውለዋል። ውጊያው እንደተፋፋመ፣ ደጃች ጎሹ በጥይት ተመትተው ወደቁ። የመሪውን መውደቅ እንደተረዳ የዳሞት ጦር ፀንቶ መመከት ተሳነው። ወዲያው የንቧይ ፒራሚድሆነ።ያለቀው አልቆቀሪው ተማረከ። 
ከምርኮኞች አንዱ፣ አዝማሪው ጣፋጭ ነበር። ጣፋጭ፣ የደጃች ጎሹ አዝማሪ ስለነበር በብዙ ጦር ሜዳ ላይ ውሏል። በጌታው ጠላት እጅ ሲወድቅም የመጀመሪያው አይደለም። በራስ ይማም ዘመንም እንዲሁ፣ ደጃዝማች ማጠንቱ የተባለ መስፍን ደጃዝማች ጎሹን ድል በነሳ ጊዜ፣ ከጌታው ጋር ተማርኮ ነበር።
ይሁን እንጂ ያኔ ዝንቡን እሽ ያለው አልነበረም። ጣፋጭ፣ የደጃች ማጠንቱ ምርኮኛ ቢሆንም፣ የእግር ብረት አልገባበትም። እንዲያውም፣ በድል አድራጊው አዳራሽ ውስጥ ያሻውን ከማንጎራጎር አልተከለከለም ነበር። በወቅቱም፣ አዝማሪው ጣፋጭ ይህንን ገላጋይ ዝማሬ አቅርቦ ነበር፤
አስረህ አንድ አትግደል፣ ደጃዝማች ማጠንቱ 
ለጀብዱ እንደሆነ፣ ይበቃል ስምንቱ።

Thursday, October 20, 2016

Under African Skies 'Ethiopia'

Under African Skies 'Ethiopia' 


ይህ  በ 1908 ዎቹ  (እ. ኤ. አ.)   የተሰራው የበቢሲ ዘጋቢ ፊልም የኢትዮጵያን ሙዚቃ ለመዳስ ይሞክራል….የተለያዩ ማስረጃዎችንና ባለሙያዎችን ያካተተ ሲሆን በዚያን ግዜ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ያለበትን ፤ደረጃ  ፤ታሪካዊ አመጣጡን እዲሁም የዘርፉ ችግሮችን ይጠቃቅሳል ፡፡
አሁን ላይ ለሚያየው የብዙ ባለሙያዎች ውህድ ዘጋቢ ፊልም በመሆኑ….ያለፉት የኪነጥበብ ሰዎቸ እና ለሙዚቃው ጥበብ  አስተዋጽኦ ላደርጉት ጥሩ መታወሻ ነው፡፡ ግን አንድ ግርምትና ጥያቄ ያጫረብኝ ነገር በሙዚቃው ዘርፍ ስሙ ከመጀመሪዎች የሚጠቀሰው እና የሙዚቃው ምልክት የሆነው ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ አለመካተቱ ነው፡፡ በርግጥ የወቅቱን ሁኔታ ለመገመትና ያለመካተቱ ጉዳይ ምክንያቱን ማወቅ ባልችልም ጥያቄ ፈጥሮብኛል ……መልሱን የሚያውቅ ካለ ስል እጠይቃለሁ ፡፡

ግሩም የሆነ ዘጋቢ በመሆኑ የወቅቱን  የኢትዮጵያ ሙዚቃን ይቃኛል የሚል እምነት ግን  አለኝ፡፡ 

Monday, May 9, 2016

“የሌላውን አስመስሎ የዘፈነን አላደንቀውም”

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
ድምፃዊው 150ሺ ብር ለበጐ አድራጐት ድርጅት ለገሰ

የትዝታው ንጉስ በሚል የሚታወቀው አንጋፋው ድምፃዊ (ዶ/ር) አርቲስት ማህሙድ አህመድ ባለፈው ሳምንት በማሪዮት ኢንተርናሽናል ሆቴልና በያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት በተለያዩ
ዝግጅቶች የ75ኛ ዓመት የልደት በዓሉን አክብሯል፡፡ የልደት በዓሉን ምክንያት በማድረግም ከልጅነት እስከ እውቀት ከተነሳቸው በርካታ ፎቶግራፎች መካከል 75 ያህሉ ተመርጠው
ለእይታ ቀርበውለታል፡፡ የፎቶ ኤግዚቢሽኑ በተከፈተበት ወቅት ባደረገው ንግግርም፤ “ብዙ የሙያ ጓደኞቼን በሞት አጥቻለሁ፤ እኔ እስካሁን በጤናና በሰላም እዚህ በመድረሴ
እግዚያብሔርን አመሰግናለሁ” ሲል የለቅሶ ሳግ ንግግሩን አቋርጦታል፡፡ አርቲስቱ ባለፈው እሁድ “ሲንደርታ ዴቨሎፕመንት ኢትዮጵያ” በተሰኘ የበጐ አድራጐት ድርጅት ውስጥ
በመገኘት ከ45 ወላጅ ያጡ ህፃናት ጋር የፋሲካን በዓል ሲያጫውታቸውና ሲዘፍንላቸው ያሳለፈ ሲሆን ውሎ ምሳ አብሯቸው ከተመገበ በኋላ ለድርጅቱ 150ሺህ ብር ለግሶ
አምባሳደራቸው እንደሚሆን ቃል ገብቶላቸዋል፡፡ በፎቶ ኤግዚቢሽኑ መክፈቻ ላይ የተገኘችው የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ ከአንጋፋው ድምፃዊ ማህሙድ አህመድ ጋር
አጭር ቃለምልልስ አድርጋለች፡፡ እነሆ፡-


75 ዓመታት በህይወት መቆየት… ሶስት መንግስታትን ማየት… በሙያ ለረጅም ጊዜ በሰው ተወድዶ መቆየት ምን ስሜት ይሰጣል?
እ…ም…ምን ስሜት ይሰጣል ነው ያልሺኝ? ከባድ ጥያቄ ነው፡፡ ስሜት እንደ ምግብ… እንደ መጠጥ ጣዕሙ በቃላት የሚገለፅ ባለመሆኑ ጥያቄው ከባድ ነው፡፡ የሆነ ሆኖ የማልዋሺሽ በጣም ደስታ ይሰማኛል፡፡እግዚአብሔር ዕድሜና ጤና ሰጥቶ ለዚህ ስላበቃኝ ደስተኛ ነኝ፡፡ 
እስካሁን በጤናህ ላይ ያጋጠመህ ችግር የለም? እድሜን ተከትለው የሚመጡ የጤና ችግሮች ይኖራሉ ብዬ ነው?
እግዚአብሔር ይመስገን እስካሁን ምንም የጤና እክል አላጋጠመኝም፤ ከዚህ በኋላ ቢያመኝም እችለዋለሁ፡፡ እንዳልሽው የሰው ልጅ እድሜው ሲገፋ የማያመው ነገር የለም፤ ከእነምሳሌው  አባቶች፣ “እርጅና ብቻህን ና” ይላሉ፡፡ እርጅና ብቻውን አይመጣም፤ ብዙ ጓዝ ያስከትላል፡፡ ቢሆንም እኔ እስካሁን ጤነኛ ነኝ፤ ከዚህ በኋላ የሚመጣውን ነገር አላውቅም፡፡ 
ለልደትህ የዛሬ ሳምንት ከአሜሪካ መምጣትህን ሰምቻለሁ፡፡ ኑሮህ ጠቅላላውን አሜሪካ ሆኗል ማለት ነው?
ኑሮዬን ጠቅልዬ አሜሪካ አላደረግሁም፡፡ እዚያ የምሄደው ለስራ ነው፡፡ እዚያ የሚያሰሩኝ ሰዎች ረጅም ቀጠሮ እየያዙ ነው የሚወስዱኝ፡፡ የተለያዩ ኮንሰርቶች እየሰራሁ ስራዬ ሲያልቅ ወደ አገሬ እመለሳለሁ፡፡ ከዛም ወደ ኢትዮጵያ ስመጣ በቀጠሮ ነው፡፡ አሁንም ለዚህ የልደት በዓል በ “አሻራ ፊልምስ” ሃላፊዎች ቀጠሮ ተይዞልኝ ነው የመጣሁት፡፡ 
ከድምፃዊ ጐሳዬ ተስፋዬ ጋር “አይባባም ሆዴ” የተሰኘ ተተኪ ማፍራትህን የሚገልጽ ነጠላ ዘፈን አውጥታችኋል፡፡ በእርግጥ ተተኪ አፍርቼአለሁ ብለህ ታስባለህ?
ማፍራቴን እርግጠኛ ነኝ፤ እንደውም ከሚጠበቀው በላይ ተተኪዎች አሉ፡፡
በምሳሌነት የምትጠቅስልኝ ይኖራሉ?
በድምፅ፣ በግጥም፣ በዜማና በአጠቃላይ ሁኔታዎች የተሻለ ነገር እየመጣ እንጂ ወደ ኋላ አልተጐተተም፡፡ ይህን ያህል ነው ብዬ ልናገረው በማልችለው ሁኔታ በቂ ተተኪ አለ፡፡ አዲሱ ትውልድ በጣም ፈጣንና ጥሩ ጥሩ የሙዚቃ ስራ እየሰራ ነው፡፡ እድገታችሁን በኔ መጠን አድርጉ ማለት አልችልም፤ ከኔ የተሻለ ይሰራሉና፡፡ አሁን ጊዜው ሙዚቃን የተሻለ አድርጐ ለመስራት አመቺ ነው፡፡ 
የአንተን ድምጽ በማስመሰል የሚዘፍኑ ወጣቶች አሉ፡፡ የተደነቅህባቸውና ያስደመሙህ ድምፃውያን አሉ?
በመጀመሪያ እኔ እኔ ነኝ፤ ማንም የእኔን አስመስሎ ሊጫወት አይችልም፡፡ ምክንያቱም መቶ በመቶ አስመስሎ መዝፈን ቀላል አይደለም፡፡ ደግሞ ቢያስመስልም አላደንቀውም፡፡ 
ለምን?
በቃ አላደንቀውም፡፡ ያ ወጣት ራሱን ማውጣት ነው ያለበት፡፡ አንድ ዘፋኝ የሌላውን አስመስሎ ሲዘፍን አላጨበጭብለትም፡፡ የእከሌን ዘፈን የሚጫወተው፣ ያ የማህሙድን ድምጽ የሚያስመስለው፣ ያ የጥላሁንን ዘፈን የሚዘፍነው እየተባለ ጣት መጠቋቆሚያ እንዲሆን አልፈልግም፡፡ ይሄ ሰው ራሱን መፍጠርና ከሌላ ሰው ድምጽ ተፅዕኖ መውጣት አለበት፡፡ እንዲህ አይነቱን ዘፋኝ ባደንቀው ምንም ስለማላመጣ ከማደንቀው ብመክረው ይሻለኛል፡፡ ምክር ብዙ ውጤት ያመጣል፡፡ 
ግን እኮ አንዳንድ ድምፃዊያን እነሱን አስመስለው ለሚዘፍኑ ወጣቶች ሽልማት እስከ መሸለም ሁሉ ይደርሳሉ?
እኔ ሌላውን ወክዬ መናገር አልችልም፤ ያ የእነሱ ስሜትና ፍላጐት ነው፡፡ የእኔን ተናግሬያለሁ፤ እንኳን መሸለም አይደለም አድናቆት አልቸርም፡፡ ጥሩ የሚሆነው ማስመሰልን ማበረታታት ይሁን ራሱን ፈልጐ እንዲያገኝ መርዳት ሁሉም የራሱን ፍርድ የሚሰጥበት ይሆናል፡፡ 
ወደፊት ከአንተ ምን አዲስ ነገር እንጠብቅ? ምን ለመስራት አስበሀል?
በቅርቡ አዲስ ነገር ብትጠብቁ ደስ ይለኛል፡፡ ምክንያቱም አዲስ ዘፈን ሰርቼ ጨርሻለሁ፡፡ 
በቅርቡ ማለት መቼ ነው?
በዚህ ቀን ነው ለማለት አልችልም፡፡ ያ ጊዜ ለእኔም ይደንቀኛል፡፡ እግዚአብሄር ያለ ቀን ብቅ ይላል፡፡ ዋናው አዳዲስ ዘፈኖች ተሰርተው መጠናቀቃቸውን አድናቂዎቼ እንዲያውቁ እፈልጋለሁ፡፡ 
የ “አሻራ ፊልምስ” ባለቤቶች በህይወት እያለህ ልደትህን ለማክበር ሲታትሩ ምን ተሰማህ?
እውነት ለመናገር በጣም ነው ደስ ያለኝ፡፡ በደስታ ነው ጥያቄያቸውን የተቀበልኩት፡፡ እነሱ እኔን ለማክበርና ልደቴን ለማሰብ ደፋ ቀና ሲሉ፣ እኔ እንዴት በደስታ አልቀበልም?! በዚህ አጋጣሚ የ“አሻራ ፊልምስ” ዳይሬክተርና ፕሮዲዩሰርን ታጠቅ ተ/ማሪያምንና የስራ ባልደረቦቹን በጣም አመሰግናለሁ፡፡ 
ዝግጅታቸውን እንዴት አገኘኸው? 
በጣም ጥሩ አድርገው ነው ያዘጋጁት፤ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡
ልደትህን አስመልክቶ በቀረበው የፎቶ ኤግዚቢሽን ላይ 75 ፎቶዎች ለእይታ ቀርበዋል፡፡  እንደው በአጠቃላይ ምን ያህል ፎቶዎች አሉ? 
ከ200 በላይ የተዘጋጁ ፎቶዎች ይኖራሉ፤ ይህ የእኔ ግምት ነው፡፡ ለስራ በየሀገሩ ስሄድ የተነሳኋቸው ፎቶዎች አልቀረቡም፡፡ በርካታ ፎቶዎች ናቸው ያሉኝ፡፡ 
በህይወትህ ይህን ሳላደርግ ቀርቻለሁ ብለህ የሚቆጭህ ነገር አለ?
በፍፁም!! እኔ ከጫማ ጠራጊነት ተነስቼ ወደ ዕውቅና ደረጃ የደረስኩ ሰው ነኝ፡፡ ተወዳጅነትና የሰው ፍቅር ተቀዳጅቻለሁ፡፡ በጣም ብዙ ነገር ያየሁና እግዚአብሔርን የማመሰግን ሰው ነኝ፤ ምንም የሚቆጨኝ ነገር የለም፡፡ በሰው ተወዶ በሰው ተከብሮ፣ ጤናና እድሜ አግኝቶ መኖር ትልቅ ፀጋ ነው፡፡ 
ከዚህ በኋላ ምን ያህል እድሜ ብትቆይ ደስ ይልሃል?
ወቸ ጉድ! ደግሞ በፈጣሪ ስራ ልግባ፣ ስንት አመት መኖር ትፈልጋለህ ትያለሽ? እሱ እንደፈቀደ ነዋ! ፈጣሪ እንደወደደ፡፡ እስከ ዛሬስ ይህን ያህል እድሜ የሰጠኝ አምላክ አይደለም እንዴ?! የኔ ታላቆችም ታናሾችም የነበሩ ብዙ ጓደኞቼ እኮ አልፈዋል፡፡ ይህ የእግዚአብሔር ስራ ነው፡፡ ስለዚህ እሱ የፈለገውን የወደደውን ያህል እድሜ ይስጠኝ፤ አለቀ፡፡
http://www.addisadmassnews.com/

Monday, December 21, 2015

“በወሮበሎች ስውር ደባ” ተሰቃይቻለሁ (ከአዲስ አድማስ)

- በየሄድኩበት ሁሉ ጥቁር ካልሲ ይጥሉብኝ ነበር
- “መድሃኒት እየሰረቀ ይሸጣል” ብለው አስወርተውብኛል

አዲስ አበባ ነው ተወልደው ያደጉት፡፡ የዕድሜያቸውን ግማሽ ያሳለፉት በውጭ አገራት ነው፡፡ በማህበረሰብ ጤና የማስተርስ ዲግሪ
ይዘው ለንደን በሚገኝ አንድ ትልቅ ሆስፒታል ውስጥ በሲኒየር ነርስነት እያገለገሉ እንደሚገኙ ይናገራሉ፡፡ አቶ ሄኖክ አያሌው ላለፉት
አራት ዓመታት “በወሮበሎች ስውር ደባ” (Gang stocking) ሲሰቃዩ እንደቆዩና በተለያዩ የራሳቸው ጥረቶች ከችግሩ ነፃ መውጣታቸውን
ይገልፃሉ፡፡ የወሮበሎች ደባ፤ አንድ ግለሰብ በወሮበሎቹ ስሙ ከጠቆረና “ብላክ ሊስት” ውስጥ ከገባ በኋላ ወደ ውድመት እንዲያመራ
የሚያደርግ ስርዓት ነው ይላሉ አቶ ሄኖክ፡፡













በወሮበሎቹ ወጥመድ ውስጥ የገባሁት በእንግሊዝ አገር ሳለሁ በተዋወቅኋት ዮዲት ጉዲት የተባለች ሴት ሰበብ ነው የሚሉት የታሪኩ
ባለቤት፤ ከእሷ ጋር ባለመግባባት ከተለያዩ በኋላ በወሮበሎቹ ጥቃት መከራቸውን ማየታቸውን ያስረዳሉ፡፡ “የወንበዴዎቹ ዓላማ
ያጠመዱትን ሰው ስም በማጥፋትና በማጠልሸት በብቸኝነት፣ በጭንቀትና በፍርሃት ማሸበር ነው ይላሉ አቶ ሄኖክ፡፡ በተከበርኩበት
ትልቅ ሆስፒታል ውስጥ “መድኃኒት እየሰረቀ ይሸጣል” ብለው አስወርተውብኛል ያሉት የታሪኩ ባለቤት፤ በየሄድኩበት ሁሉ ጥቁር ካልሲ
ይጥሉብኝ ነበር… በማለት የደረሰባቸውን ያስረዳሉ፡፡ ባለፈው አራት ዓመት የደረሰባቸውን ስቃይም፣ “የዲያስፖራው ስውር ደባ” በተሰኘ
መፅሃፋቸው ተርከውታል፡፡ መፅሀፉ “The Jaws of Evil” በሚልም ወደ እንግሊዝኛ ተተርጉሞ ባለፈው ሳምንት ከአማርኛው ጋር
ተመርቋል፡፡ የ49 ዓመቱ ጐልማሳ አቶ ሄኖክ አያሌው “የወሮበሎች ስውር ደባ” በሚሉት ጉዳይ ዙሪያ ከአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት
ዮሴፍ ጋር ተከታዩን ሰፊ ቃለ-ምልልስ አድርገዋል፡፡

Monday, November 16, 2015

’’ዜጎቿን ለማስራብ እየተጋች ያለች ሀገር ኢትዮጵያ !’’


ሰለሞን ዮሃንስ
እኔ ርሀብን የማውቀው ለሰዓታት ነው:: ለዚያውም ምን ያህል ሰዓት እህል ሳልቀምስ መቆየት እችላለሁ ብዬ የሞከርኳት የቅብጠት ቆይታ ፡፡ያጥወለመለኝን ፤ማይትያቃተኝን ፤ያዘፈዘፈኝን ፍጹም ያዛለኝን የያኔው ርሃቤ ከዛሬው ርሃብ ውሎ ካደረበትና የሚላስና የሚቀመሰውን ካየ ቀናት የተቆጠሩበት ወገኔ ጋር ፈጽሞ ለንጽጽር የሚቀርብ አይደለም፡፡ እኔስ ያኔ ያገኘሁትን አግበስብሼ ነፍሴ መለስአለች ፡፡
ዛሬስ ወገኔማ ማሳው ደርቆ ፤ጎተራው ባዶ ሆኖ ተስፋ በሌለው ውል የመጨረሻ ቀኑን ይቆጥራል፡፡
ርሃብ ስንት ቀን ይፈጃል? ብዬ ልፈላሰፍ አይዳዳኝም፤ ወገኔ የሚላስ የሚቀመስ አጥቶ አጥንቱ እተቆጠረ አይኑ እየፈጠጠ ሰውነቱ ተስለምሞልሞ መጨረሻውን ይጠብቃል  …እንስሳቱማ መንገዱን ጠርገውለታል ፡፡
ለዚህ ደግና ኩሩ አፈርገፊ ህዝብ ይህ አይገባውም ነበር ፡፡
ይህ ደግ ህዝብ የሚቀጣው ለምን ይሆን ???
ዛሬም የዩቱ የሙዚቃ ባንድ   አባለቱንቱን ወዴት ናችሁ  ? ቦብ ጌልዶፍስ ምነው ዝም አልክ ? ማይክል ጃክሰን  ሆይ መቃብሩን ፈንቅልና ከሙያ አጋሮችህ ጋር ድረስልን እንበለው?
ምን አይነት ጉድ ነው የተጠናወተን ?
ማነው እንባውን እያዘራ ኢትዮጵያን ርሃብና ርዛት ከምድርሽ አይጥፋ ብሎ አምርሮ የረገማት?
ምን አይነት ክፉ ቀን ነው ተጣብቶ አለቅ ያለን ?
ይሄ ሀገሩን የሚመግበው ገበሬ የማይደክመው ፍጡር ዛሬ ተረታሁ ብሎ ይጣራል የሰሚ ያለህ እያለነው ፡፡ ጎታው ባዶ ሆኖ መሬቱ ደርቆ የሚውዳቸው እንስሳቱ ሞተውበት ድፍርስ እንባውን እያነባ ባዶ ማረሻ ይዞ ተስፋው ተሟጦ የሚመጣውን ይጠባበቃል፡፡
ያች ምስኪን እናት የልጆቿ የርሃብ እሪታ ጸንቶባት ሰቆቃ መስማት ተስኗት ከልጆቼ በፊት እኔን አስቀድመኝ ብላ ፈጣሪዋን ብትማጸንም  ልጆቿን በሞት መነጠቅ አልቀረላትም፡፡
እሷም የታጠፈ አንጀትዋን መቀነት አድርጋ እንባዋን ታዘራለች፡፡
እኛስ ?
እኛ ደግሞ እዚህ በስሜታዊነት ብቻ ማዶለማዶ ሆነን በቃላትና ቁጥርን መባስተባበል ተጠምደን
ዒላማ አልባ የደነበሸ ጥይት እንተኳኮሳለን ፤
ድርቅ ሆነ ርሃብ ፤
10 ሆነ 15 ሚሊየን ፤
ሰሜን ሆነ ደቡብ ፤
ክርክራችን ለዚህ በርሃብ አንጀቱ ለታጠፈ ኢትዮጵያዊ ምን ይጠቅመወቀል እንጀራ ውይስ ውሃ ይሆነዋል?
የሰው ልጅ ክቡር እየወደቀ ነው፡፡
ሰው የሚበላ ይፈልጋል በውሃ ጥም ጉሮሮው ደርቋል…ርሀብ እሞሸለቀው ነው ፡፡

ይህ ደግና ኩሩ ህዝብ 90 ሚሊየን ቤተሰቡን በጫንቃው የተሸከመው ታታሪ ገበሬ አቅቶተታል ፡፡

የደፈረሰ እንባውን የሚያብስለት፤ርሀቡን የሚያስታግስለት ወገን ይፈልጋል ፡፡
ምዕራብያኑን ’’የስንዴያለህ  ???’’ ብለን በራቸውን ብናንኳኳ በራሰቸው የቤት ስራና ቅድሚያ በሚሰጡት ነገር ተጠምደዋልና ፤ ወደውስጣችን እንመለስ ፡፡
ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን ወገናችን ተርበቧል ፤
ይህ ደግ ህዝብ አቅቶታል፡፡
ይህ ደግ ህዝብ እኛኝ ይሻል፡፡
አዎእኛኝይሻል …..ጎራውን እንተውውና …ለዚህ ጨዋና ኩሩ ህዝብ አሁኑኑ እንድረስለት፡፡
አሁኑኑ !!!!!
’’ዜጎቿን ለማስራብ እየተጋች ያለች ሀገር ኢትዮጵያ !’’……. ከሚል ስላቅ ለመዳን ትልቅ የቤት ስራ ይጠበቅብናል፡፡
መቼም ኢትዮጵያ ልጆቿን ለማስራብ እነደማትተጋ ይታወቃል፡፡