Wednesday, July 31, 2013

የኮኖጎዋ ብራዛቪል የኢትዮጵያንና ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክን ጨዋታ ልታስተናግድ ነው

(ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያና  ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የሚያደርጉት ጨዋታ ኮንጎ ብራዛቪል ላይ እንዲደረግ ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን/ፊፋ/ መወሰኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ገለፀ ።

የሁለቱ አገራት ጨዋታ ጷጉሜ  ወር ላይ በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ዋና ከተማ  ባንጉይ መካሄድ የነበረበት ቢሆንም ፥  በአገሪቱ ያለው  የፀጥታ ሁኔታ ጨዋታውን ለማካሄድ የሚያስችል ባለመሆኑ ተለዋጭ አስተናጋጅ አገር ሲፈላለግ ቆይቷል ።

በፈረንጆቹ መስከረም 7  በብራዛቪል  የሚካሄደውን የኢትዮጵያና  የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጨዋታንም የሚዳኙ አራት ዳኞች ከአልጄሪያ  መመረጣቸውንም  ፊፋ  ጨምሮ ገልጿል ።

ስለጨዋታው ያነጋገርናቸው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዋና  አሰልጣኝ አቶ ሰውነት ቢሻው ውደድሩ  የሚካሄድበት ቦታ ሞቃታማ ቢሆንም ጠንከረን በመስራት  ግባችንን  አንመታለን ብለዋል ።

አቶ ሰውነት ጨምረውም ጨዋታው በኬኒያ አልያም በኡጋንዳ ቢካሄድ ኖሮ ለኢትዮጵያ  የተሻለ እንደነበር ነው የተናገሩት ።

No comments:

Post a Comment